መዝሙር 15
15
መዝሙር 15
የእግዚአብሔር ቤተኛ
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል?
በተቀደሰው ኰረብታህስ ማን መኖር ይችላል?
2አካሄዱ ንጹሕ የሆነ፣
ጽድቅን የሚያደርግ፤
ከልቡ እውነትን የሚናገር፤
3በምላሱ የማይሸነግል፤
በባልንጀራው ላይ ክፉ የማይሠራ፤
ወዳጁን የማያማ፤
4ነውረኛ በፊቱ የተናቀ፤
እግዚአብሔርን የሚፈሩትን ግን የሚያከብር፤
ዋጋ የሚያስከፍለውም ቢሆን፣
ቃለ መሐላውን የሚጠብቅ፤
5ገንዘቡን በዐራጣ የማያበድር፣
በንጹሓን ላይ ጕቦ የማይቀበል፤
እነዚህን የሚያደርግ፣
ከቶ አይናወጥም።
Currently Selected:
መዝሙር 15: NASV
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.