YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 15

15
መዝሙር 15
የእግዚአብሔር ቤተኛ
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል?
በተቀደሰው ኰረብታህስ ማን መኖር ይችላል?
2አካሄዱ ንጹሕ የሆነ፣
ጽድቅን የሚያደርግ፤
ከልቡ እውነትን የሚናገር፤
3በምላሱ የማይሸነግል፤
በባልንጀራው ላይ ክፉ የማይሠራ፤
ወዳጁን የማያማ፤
4ነውረኛ በፊቱ የተናቀ፤
እግዚአብሔርን የሚፈሩትን ግን የሚያከብር፤
ዋጋ የሚያስከፍለውም ቢሆን፣
ቃለ መሐላውን የሚጠብቅ፤
5ገንዘቡን በዐራጣ የማያበድር፣
በንጹሓን ላይ ጕቦ የማይቀበል፤
እነዚህን የሚያደርግ፣
ከቶ አይናወጥም።

Currently Selected:

መዝሙር 15: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in