YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 14

14
መዝሙር 14
አምላክ የለሽ ሰዎች
14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።
1ሞኝ#14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣
“እግዚአብሔር የለም” ይላል።
ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤
በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።
2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣
እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።
3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤
በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤
አንድ እንኳ፣
መልካም የሚያደርግ የለም።
4 የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣
ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣
ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?
5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤
እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።
6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤
እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።
7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!
እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣
ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

Currently Selected:

መዝሙር 14: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in