መዝሙር 14
14
መዝሙር 14
አምላክ የለሽ ሰዎች
14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።
1ሞኝ#14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣
“እግዚአብሔር የለም” ይላል።
ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤
በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።
2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣
እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።
3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤
በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤
አንድ እንኳ፣
መልካም የሚያደርግ የለም።
4 የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣
ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣
ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?
5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤
እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።
6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤
እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።
7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!
እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣
ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።
Currently Selected:
መዝሙር 14: NASV
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.