BibleProject | የዘወረደ ምልከታዎችSample

ተስፈኝነት ሁኔታዎች ተስተካክለው ለበጎ የሚሆኑበትን መንገድ ለማየት መምረጥ ነው። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ተስፋ ግን በሁኔታዎች የተመረኮዘ አይደለም። እንደውም፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ተስፋ ያላቸው ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ነገሮች እንደሚስተካከሉ የሚያመለክት ምንም ማስረጃ የሌለባቸውን ከባባድ ወቅቶች ያሳልፋሉ፤ ይሁን እንጂ አሁንም ተስፋ ለማድረግ ይመርጣሉ። ለምሳሌ፣ የእስራኤል ነቢይ የሆነው ሚክያስ ኢፍትሃዊነትና ክፋት በተስፋፋበት ዘመን ይኖር ነበር፤ ግን ደግሞ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርጎ ነበር።
ያንብቡ፦
ሚክያስ 7÷6-8
ምልከታዎን ያስፍሩ፡
ሚክያስ በቁጥር 6 የሚዘረዝራቸውን አንዳንድ ችግሮችና በቁጥር 7 እና 8 የሚሰጠውን ምላሽ ያስተውሉ። በዚህ ጊዜ በዙሪያዎ ካሉ ችግሮች አንዳንዶቹ ምንድን ናቸው? የሚክያስ ምላሽ ዛሬ የሚያበረታታዎ ወይም የሚሞግትዎ እንዴት ነው?
ሚክያስ ለእግዚአብሔር የጸለየውን ጸሎት መልሰው ለመጸለይ ጥቂት ጊዜ ይውሰዱ። እግዚአብሔር ይሰማዎታል።
Scripture
About this Plan

ባይብል ፕሮጀክት የዘወረደ ተከታታይ ትምህርቶችን ያዘጋጀው ግለሰቦች፣ ቡድኖች እንዲሁም ቤተሰቦች ዘወረደን፣ ማለትም የኢየሱስን ወደ ምድር መምጣት እንዲያከብሩ ለማነሳሳት ነው። ተስፋ፣ ሰላም፣ ሀሴት እና ፍቅር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጉማቸው ምን እንደሚመስል ተሳታፊዎች እንዲያጤኑ ለማገዝ እንዲጠቅም፣ ይህ የአራት ሳምንት የጥናት እቅድ የአኒሜሽን ቪዲዮዎችን፣ አጫጭር ማጠቃለያዎችን እና ሃሳብ ጫሪ ጥያቄዎችን አካቷል። እነዚህ አራት መንፈሳዊ እሴቶች እንዴት በኢየሱስ በኩል ወደ አለም እንደመጡ ለመረዳት፣ ይህን የጥናት እቅድ ይምረጡ።
More
Related Plans

Unboxed: Built on Purpose

Cherished & Chosen: A 7-Day Challenge for Single Women

Love at Work

Dear Black Woman, You Are Not Alone in Your Grief

Relentless Love: Reflections on the Book of Jonah

Holy Spirit - Breath of God

Boundaries: A Biblical Perspective

Journey Through Revelation

Journey Through 1 & 2 Peter and Jude
