YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 13

13
መዝሙር 13
በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ?
ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው?
2ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣
ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው?
ጠላቴስ በእኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ድረስ ነው?
3 እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ተመልከት፤
ስማኝም፤
የሞት እንቅልፍ እንዳልተኛ ዐይኖቼን አብራ፤
4በዚህም ጠላቴ፣ “አሸነፍሁት” እንዳይል፣
ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ።
5እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤
ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።
6ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣
ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።

Currently Selected:

መዝሙር 13: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in