YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 1

1
አንደኛ መጽሐፍ
ከመዝሙር 1–41
መዝሙር 1
ሁለቱ መንገዶች
1በክፉዎች ምክር የማይሄድ፣
በኀጢአተኞች መንገድ የማይቆም፣
በፌዘኞችም ወንበር የማይቀመጥ፣
ሰው ብፁዕ ነው፤
2ነገር ግን ደስ የሚሰኘው በእግዚአብሔር ሕግ ነው፤
ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል።
3እርሱም በወራጅ ውሃ ዳር እንደ ተተከለች፣
ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣
ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤
የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
4ክፉዎች ግን እንዲህ አይደሉም፤
ነገር ግን ነፋስ ጠራርጎ እንደሚወስደው፣
ገለባ ናቸው።
5ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ ፊት፣
ኀጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር መቆም አይችሉም፤
6 እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ይጠብቃልና፤
የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።

Currently Selected:

መዝሙር 1: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy