መጽ​ሐፈ ጥበብ 14

14
የጣ​ዖት ከን​ቱ​ነት
1ዳግ​መ​ኛም ሰው በክፉ የባ​ሕር ማዕ​በል መካ​ከል ይሄድ ዘንድ ወድዶ በመ​ር​ከብ ላይ በወጣ ጊዜ ከም​ት​ሸ​ከ​መው ከመ​ር​ከ​ቢቱ፥ ከሚ​ዋ​ረ​ደ​ውና ከሚ​ደ​ክ​መው እን​ጨት ይለ​ም​ናል። 2ያን ጣዖት ትርፍ በመ​ው​ደድ ሠር​ቶ​ታ​ልና፥ ብል​ህም በብ​ል​ሀቱ ሠር​ቶ​ታ​ልና። 3አብ ሆይ፥ ያንተ አመ​ራር ግን ሁሉን ትሠ​ራ​ራ​ለች፤ በባ​ሕር ውስጥ መን​ገ​ድን፥ በሞ​ገ​ድም መካ​ከል ጽኑ መተ​ላ​ለ​ፊ​ያን ሰጥ​ተ​ሃ​ልና። 4ወደ መር​ከብ በማ​ው​ጣት፥ ዳግ​መ​ኛም ያለ ጥበብ ሰውን በባ​ሕር ላይ በማ​ሳ​ለፍ በእ​ው​ነት ሁሉን ማዳን እን​ደ​ሚ​ቻ​ልህ ታሳይ ዘንድ፥ 5የጥ​በ​ብህ ሥራው ስን​ፍና እን​ዳ​ይ​ሆን ትወ​ዳ​ለህ፥ ስለ​ዚህ ሰዎች ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን በተ​ና​ቀና በተ​ዋ​ረደ እን​ጨት ተማ​ም​ነው በታ​ላ​ቅና በታ​ናሽ መር​ከብ በሞ​ገዱ መካ​ከል ተሻ​ግ​ረው ይድ​ናሉ።
6ቀድ​ሞም ትዕ​ቢ​ተ​ኞች ረዓ​ይት#“ረዓ​ይት” ግዙ​ፋን ወፍ​ራ​ሞች ረዥ​ሞች ማለት ነው። በጠፉ ጊዜ የዓ​ለም ተስፋ በመ​ር​ከብ ተጭ​ኖና ተጠ​ግቶ ዳነ፥ በእ​ጅ​ህም ተመ​ርቶ የሰ​ውን ዘርዕ ለዓ​ለም አተ​ረፈ። 7ይህ መር​ከብ ጽድቅ ይሠ​ራ​በት ዘንድ ተባ​ር​ኳ​ልና። 8በእጅ የተ​ሠ​ራው ግን የሚ​ጠፋ ሲሆን አም​ላክ ስለ ተባለ የተ​ረ​ገመ ነው፤ የሠ​ራ​ውም ይህን በመ​ሥ​ራቱ ርጉም ነው። 9በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ክፉና ክፋቱ በት​ክ​ክል ተጠ​ል​ተ​ዋ​ልና፥ 10የተ​ሠ​ራው ሥራ ከሠ​ሪው ጋር ይፈ​ረ​ድ​በ​ታ​ልና። 11ስለ​ዚ​ህም በአ​ሕ​ዛብ ጣዖ​ታት ምር​መራ ይደ​ረ​ጋል። ፍጥ​ረ​ትን ለማ​ጥ​ፋት ለሰ​ዎ​ችም ነፍ​ሳት መሰ​ና​ክል፥ ለአ​ላ​ዋ​ቂ​ዎች ሰዎች እግ​ሮ​ችም ወጥ​መድ ሆኖ ተሠ​ር​ት​ዋ​ልና፥
ጣዖ​ትን ማም​ለክ የዝ​ሙት መጀ​መ​ሪያ ስለ መሆኑ
12የዝ​ሙት መጀ​መ​ሪ​ያዋ ጣዖ​ትን የመ​ሥ​ራት ዐሳብ ነውና፥ እር​ሱ​ንም ማግ​ኘት የሕ​ይ​ወት ጥፋት ነው። 13ከጥ​ንት ጀምሮ አል​ነ​በ​ረ​ምና ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም አይ​ኖ​ር​ምና። 14ተነ​ጥ​ቀው የመ​ሄ​ዳ​ቸ​ውን ፍጻሜ የሚ​ያ​ፋ​ጥን ስለ​ሆነ በከ​ንቱ ሰው ምክ​ን​ያት ጣዖት ወደ​ዚህ ዓለም ገባ። ከዚ​ህም በኋላ ጣዖት መሥ​ራ​ትን ዐሰቡ። 15ልጁ ሕፃን ሳለ ፈጥኖ በሞት ስለ ተነ​ጠቀ አባቱ ላንድ ልጁ ይጨ​ነ​ቅና ያለ​ቅስ ነበ​ርና፥ ቀድሞ ለሞ​ተው ልጁ ምስል ሠራ​ለት፥ ዛሬ ግን እንደ አም​ላክ አድ​ር​ገው አከ​በ​ሩት። ለኀ​ጢ​አት የተ​ገዙ ሰዎ​ችም በስ​ውር በዓል አደ​ረ​ጉ​ለት፥ የም​ሥ​ጢር መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም ሠዉ​ለት። 16ከዚህ በኋላ በዘ​መን መራቅ የበ​ደ​ልና የዝ​ን​ጋዔ ልማድ ሥር​ዐት ሆኖ ተያዘ፥ እንደ ሕግም አድ​ር​ገው ጠበ​ቁት፥ በክ​ፉ​ዎች መኳ​ን​ንት ትእ​ዛ​ዝም ጣዖ​ታ​ትን አመ​ለ​ኳ​ቸው። 17በሩቅ ስለ​ሚ​ኖሩ ፊት ለፊት ሊያ​ከ​ብ​ሯ​ቸው የማ​ይ​ቻ​ላ​ቸ​ውን ሰዎች ቅርፁ በሩቅ ያለ መል​ካ​ቸ​ውን ቀረፁ፥ በእ​ነ​ርሱ ዘንድ ክቡር ለሚ​ሆን ለን​ጉ​ሡም ግልጥ የሆነ ምስል ሠሩ​ለት። የሌ​ለ​ው​ንም እን​ዳለ አድ​ር​ገው በት​ጋት ይለ​ም​ናሉ። 18ስሕ​ተ​ታ​ቸ​ው​ንም ያላ​ወቁ ሰዎች በአ​ም​ል​ኮ​ታ​ቸው ጸኑ። የጥ​በ​በ​ኛ​ው​ንም ክብር ወደ ጣዖት አም​ልኮ መለሱ። 19ዳግ​መኛ ገዥ​ውን ንጉሥ አድ​ልቶ ደስ ያሰ​ኘው ዘንድ የሚ​ወድ አለ። ባማ​ረና በተ​ሻለ ሁኔታ ምስ​ሉን ለመ​ሥ​ራት ተራ​ቅ​ቆ​አ​ልና። 20በሥ​ራ​ውም መልክ ማማር ደስ ስላ​ላ​ቸው ብዙ ሰዎች በዚህ ተሳቡ፥ ከጥ​ቂት ቀን አስ​ቀ​ድሞ በት​ንሽ ክብር የነ​በረ ሰው​ንም ዛሬ እንደ አም​ላክ አደ​ረ​ጉት። 21በች​ግር ወይም በግድ ሰው ሁሉ ተገ​ዝ​ት​ዋ​ልና ይህ ለሰው መሰ​ና​ክ​ልን ሆነ፤ ከእ​ነ​ርሱ ጋር አን​ድ​ነት የሌ​ለ​ውን የፈ​ጣ​ሪን ስም ለሚ​ጠ​ቀ​ሙ​ባ​ቸው ለድ​ን​ጋ​ይና እን​ጨት አድ​ር​ገ​ው​ታ​ልና።
የአ​ም​ልኮ ጣዖት ውጤት
22ዳግ​መ​ኛም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ካለ​ማ​ወ​ቃ​ቸው የተ​ነሣ ስሕ​ተ​ታ​ቸው አል​በ​ቃ​ቸ​ውም፥ ነገር ግን በታ​ላቅ ሰልፍ ሳሉ በስ​ን​ፍ​ና​ቸው ይኖ​ራሉ። ይህን ያህል ክፉ የሆ​ነ​ው​ንም ታላቅ አደ​ረጉ፥ ሰላም ብለ​ውም ጠሩት። 23ልጆ​ቻ​ቸ​ውን የሚ​ሠዉ አሉና፤ የተ​ሰ​ወረ ምሥ​ጢ​ር​ንም ያደ​ር​ጋሉ፥ በልዩ ሥር​ዐ​ትም እየ​ተ​ቅ​በ​ዘ​በዙ ያስ​ባሉ። 24ሕጋ​ቸ​ው​ንና ጋብ​ቻ​ቸ​ውን አል​ጠ​በ​ቁም፤ ነገር ግን ባል​ን​ጀራ ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ይገ​ድ​ለ​ዋል፤ ያም ባይ​ሆን ያባ​ብ​ለ​ዋል፥ በሽ​ተ​ኛም ያደ​ር​ገው ዘንድ ተስፋ ይሰ​ጠ​ዋል። 25ሥራ​ዎ​ቻ​ቸው ሁሉ ደም ከማ​ፍ​ሰ​ስና ነፍስ ከመ​ግ​ደል ጋር፥ ከመ​ስ​ረ​ቅም ጋር፥ ከሐ​ሰ​ትና ከጥ​ፋት፥ ምስ​ጋ​ና​ንም ከማ​ጕ​ደል ጋር፥ ካለ​ማ​መ​ንም ጋር፥ ከመ​ሐ​ላና በጎ​ውን ሰው ከማ​ወክ ጋር፥ 26ዋጋን ካለ​ማ​ሰብ ጋር፥ ሰው​ነ​ትን ከማ​ስ​ተ​ዳ​ደፍ ጋር፥ ፍጥ​ረ​ት​ንም ከመ​ለ​ወጥ ጋር፥ የጋ​ብ​ቻን ሥር​ዐት ከማ​ፍ​ረስ ጋር፥ ከም​ን​ዝ​ርና ከር​ኵ​ሰት ጋር፥ የተ​ቀ​ላ​ቀለ ነው። 27ስም የሌ​ላ​ቸው ጣዖ​ቶ​ችን ማም​ለክ የክ​ፋት ሁሉ መጀ​መ​ሪያ ነውና፥ የፍ​ጻ​ሜ​ውም ምክ​ን​ያት ነውና። 28የሚ​ያ​መ​ል​ኳ​ቸው ሰዎች እንደ እነ​ዚህ ደስ ቢላ​ቸው አእ​ም​ሮ​አ​ቸ​ውን ያጣ​ሉና። ያም ባይ​ሆን በሐ​ሰት ትን​ቢት ይና​ገ​ራሉ፥ ያም ባይ​ሆን ይሙት በቃ​ውን ያድ​ናሉ፥ ያም ባይ​ሆን ፈጥ​ነው ይም​ላሉ። 29ቃልና ዕው​ቀት ያላ​ቸው እነ​ዚህ ሁሉን እን​ደ​ሚ​ያ​ውቅ እንደ ፈጣሪ አድ​ር​ገው ነፍስ የሌ​ለው ሐሰ​ተ​ኛና ድዳ ጣዖ​ትን ይታ​መ​ናሉ፥ ቢም​ሉም እን​ደ​ሚ​ፈ​ረ​ድ​ባ​ቸው አያ​ስ​ቡም። 30እው​ነ​ተኛ ፍርድ በአ​ን​ድ​ነት ያገ​ኛ​ቸ​ዋል፥ ጣዖ​ቱን በተ​መ​ለ​ከቱ ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክፉ ነገ​ርን ዐስ​በ​ዋ​ልና፥ የፈ​ጣ​ሪን እው​ነት አቃ​ል​ለው በግ​ፍና በሐ​ሰት ምለ​ው​በ​ታ​ልና። 31በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው የተ​ፈ​ረ​ደ​ባ​ቸ​ውን ፍርድ ለማ​ስ​ተ​ላ​ለፍ ነው እንጂ ኀይ​ሉን ይገ​ል​ጥ​ብ​ናል ሲሉ የማሉ አይ​ደ​ለ​ምና፤ እን​ግ​ዲህ ሁል​ጊዜ ሰውን በሚ​በ​ድሉ ሰዎች ወን​ጀል ላይ ፍርድ ትም​ጣ​ባ​ቸው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ