መጽ​ሐፈ ኢዮብ 34

34
ኤል​ዩስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እው​ነ​ተኛ ፈራጅ መሆን እንደ ተና​ገረ
1ኤል​ዩስ ደግሞ መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“እና​ንተ ጥበ​በ​ኞች፥ ቃሌን ስሙ፤
እና​ን​ተም ዐዋ​ቂ​ዎች፥ መል​ካም ነገ​ርን አድ​ምጡ።
3ጆሮ ቃልን ትለ​ያ​ለ​ችና፥
ጕሮ​ሮም የመ​ብ​ልን ጣዕም ይለ​ያል።
4ፍር​ድን ለራ​ሳ​ችን እን​ም​ረጥ፤
በመ​ካ​ከ​ላ​ች​ንም ምን እን​ደ​ሚ​ሻል እን​ወቅ።
5ኢዮብ እን​ዲህ ብሎ​አ​ልና፦ እኔ ጻድቅ ነኝ፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ፍር​ዴን አስ​ወ​ገደ፤
6ፍር​ዴን ሐሰ​ተኛ አደ​ረ​ገ​ብኝ፤ #በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
በደ​ልም ሳይ​ኖ​ር​ብኝ በግ​ፍዕ መከ​ራን እቀ​በ​ላ​ለሁ።
7መሣ​ለ​ቅን እንደ ውኃ የሚ​ጠ​ጣት፥
እንደ ኢዮብ ያለ ሰው ማን ነው?
8ፈጽሞ ያል​በ​ደለ፥
ግፍን ከሚ​ሠ​ሩም ጋር ያል​ተ​ባ​በረ፥
ከኃ​ጥ​ኣ​ንም ጋር ያል​ሄደ፥ ማን ነው?
9ሰው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጕብ​ኝት ሲኖ​ረው
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አይ​ጐ​በ​ኘ​ውም አት​በል።
10“ሰለ​ዚህ እና​ንተ አእ​ምሮ ያላ​ቸሁ ሰዎች ስሙኝ፤
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ዘንድ ትበ​ድሉ ዘንድ አት​ው​ደዱ።
ሁሉን በሚ​ችል አም​ላክ ፊትም ጻድ​ቁን አታ​ው​ኩት።
11ለሰው ሁሉ እንደ ሥራው ይመ​ል​ስ​ለ​ታል፥
ሰው​ንም እንደ መን​ገዱ ያገ​ኘ​ዋል።
12በእ​ው​ነት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ግፍ እን​ደ​ሚ​ሠራ ታደ​ር​ገ​ዋ​ለ​ህን?
ወይስ ምድ​ርን የፈ​ጠረ ሁሉን የሚ​ችል አም​ላክ ፍር​ድን ያጣ​ም​ማ​ልን?
13ከሰ​ማይ በታች ያለ​ውን ዓለም፥
በው​ስ​ጡም ያሉ​ትን ነገ​ሮች ሁሉ የፈ​ጠረ ማን ነው?
14በእ​ርሱ ያለ መን​ፈ​ሱን፥
ሊያ​ጸ​ናና ሊይዝ ቢወ​ድድ፥
15ሥጋ ለባሽ ሁሉ በአ​ን​ድ​ነት ይሞ​ታል፥
ሟችም ሁሉ ወደ ተፈ​ጠ​ረ​በት መሬት ይመ​ለ​ሳል።
16ያለ​ዚያ ግን ተመ​ከር፥ ይህ​ንም ስማ፤
የን​ግ​ግ​ሬ​ንም ቃል አድ​ምጥ።
17ግፍን የሚ​ጠላ፥ ክፉ​ዎ​ች​ንም የሚ​ያ​ጠፋ፥
ለዘ​ለ​ዓ​ለም ጻድቅ ነው።
18ንጉ​ሡን፦ በደ​ለኛ ነህ የሚ​ለው፥
መኳ​ን​ን​ቱ​ንም፦ ክፉ​ዎች ናችሁ የሚ​ላ​ቸው ኀጢ​አ​ተኛ ነው
19እርሱ ግን የክ​ቡ​ርን ሰው ፊት አያ​ፍ​ርም።#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
ለታ​ላ​ቁም ክብር መስ​ጠ​ትን አያ​ው​ቅም፥ ከፊ​ታ​ቸ​ውም አይ​ሸ​ሽም።#በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም።
20የሚ​ጮ​ኸ​ው​ንና ሰውን የማ​ይ​ሰ​ማ​ውን ከንቱ ነገር ያገ​ኘ​ዋል፥
በድ​ሆች ላይ ክፉ አድ​ር​ጎ​አ​ልና።#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
21እርሱ የሰ​ዎ​ችን ሥራ ይመ​ረ​ም​ራል፥
ከሚ​ሠ​ሩ​ትም ሁሉ ከእ​ርሱ የሚ​ሰ​ወር ምንም የለም።
22ኀጢ​አ​ትን የሚ​ሠሩ የሚ​ሰ​ወ​ሩ​በት ቦታ የለም።
23ሁሉን ከሚ​ያይ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አያ​መ​ል​ጡ​ምና።#ከግ​ሪክ ሰብ. ሊ. እና ከዕብ. ይለ​ያል።
24እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ ታች ወደ ሰዎች ይመ​ለ​ከ​ታል፥
ሊመ​ረ​መሩ የማ​ይ​ችሉ ነገ​ሮ​ችን ሁሉ፥
ቍጥር የሌ​ላ​ቸ​ውን የተ​ከ​በ​ሩ​ት​ንና ድን​ቆ​ች​ንም ያስ​ተ​ው​ላል።
25ሥራ​ቸ​ውን ያው​ቃል፥
በእ​ነ​ር​ሱም ላይ ሌሊ​ትን ያመ​ጣል፥ መከ​ራ​ንም ያጸ​ና​ባ​ቸ​ዋል።
26ኃጥ​ኣ​ንን ያጠ​ፋ​ቸ​ዋል፥
ጻድ​ቃን ግን በፊቱ ናቸው።
27ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ፈቀቅ ያሉ፥
ፍር​ዱን አያ​ው​ቁም።
28እር​ሱም የድ​ሆ​ችን ጩኸት በእ​ነ​ርሱ ላይ ይመ​ል​ሳል፥
የች​ግ​ረ​ኞ​ች​ንም ልቅሶ ይሰ​ማል።
29“እርሱ ዕረ​ፍ​ትን ይሰ​ጣል፤
የሚ​ፈ​ር​ድስ ማን ነው?
በሕ​ዝብ ወይም በሰው ዘንድ ፊቱን ቢሰ​ውር የሚ​ያ​የው ማን ነው?
30ስለ ሕዝ​ቡም ክፋት፥
ግብዝ ሰውን ያነ​ግ​ሣል።
31“ኀያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን፦ እን​ዲህ የሚል አለ፥
እኔ በረ​ከ​ትን ተቀ​በ​ልሁ፥
መያ​ዣ​ው​ንም አል​ወ​ስ​ድም።
32እኔ ራሴ አያ​ለሁ፥
ኀጢ​አ​ት​ንም ሠርቼ እንደ ሆነ፥ ሐሰ​ት​ንም ተና​ግሬ እንደ ሆነ፥#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
ደግሜ እን​ዳ​ል​ሠራ አንተ አሳ​የኝ።
33በውኑ አንተ ከእኔ ትርቅ ዘንድ፥
እኔ ከአ​ንተ የተ​ቀ​በ​ል​ሁት አለን?
አንተ ትመ​ር​ጣ​ለህ እንጂ እኔ አይ​ደ​ለ​ሁ​ምና፤
ስለ​ዚህ የም​ታ​ው​ቀው ካለ ተና​ገር።
34የልብ ጥበ​በ​ኞች እን​ዲህ ይላ​ሉና፦
ጠቢብ ሰው ነገ​ሬን ይሰ​ማ​ኛል።
35ኢዮብ እንደ ጠቢብ በዕ​ው​ቀት አይ​ና​ገ​ርም፥
ቃሉም እንደ ምሁር አይ​ደ​ለም።
36ነገር ግን ኢዮብ ሆይ፥ ተማር።
እንደ ሰነ​ፎ​ችም አት​መ​ልስ፥
37በኀ​ጢ​አ​ቶ​ችህ ላይ እን​ዳ​ት​ጨ​ምር፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. በብዙ።
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ብዙ መና​ገር በደል ይሆ​ን​ብ​ሃል።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ