መጽ​ሐፈ ኢዮብ 35

35
ኢዮብ ራሱን በማ​ጽ​ደቁ ኤል​ዩስ እንደ ተቃ​ወመ
1ኤል​ዩ​ስም ደግሞ መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“አንተ ተዋ​ቅ​ሰህ ምን ትላ​ለህ?
ወይስ፦ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እኔ ጻድቅ ነኝ የም​ትል አንተ ማን ነህ?
3ኀጢ​አት ብሠ​ራስ ምን አደ​ር​ጋ​ለሁ? ትላ​ለህ።#በዕብ. ልዩ ነው።
4እኔ ለአ​ን​ተና ለሦ​ስቱ ወዳ​ጆ​ችህ እመ​ል​ሳ​ለሁ።
5ወደ ሰማይ ተመ​ል​ከት፥ እይም፤
ደመ​ናም ከአ​ንተ በላይ ምን ያህል ከፍ እን​ዳለ ዕወቅ።
6ኀጢ​አት ብት​ሠራ በእ​ርሱ ላይ ምን ታደ​ር​ጋ​ለህ?
ብዙም ብት​በ​ድል ምን ማድ​ረግ ትች​ላ​ለህ?
7ጻድ​ቅስ ብት​ሆን ምን ትሰ​ጠ​ዋ​ለህ?
ወይስ ከእ​ጅህ ምንን ይቀ​በ​ላል?
8እንደ አንተ ያለ​ውን ሰው ክፋ​ትህ ይጎ​ዳ​ዋል፤
ለሰ​ውም ልጅ ጽድ​ቅህ ይጠ​ቅ​መ​ዋል።
9ከግ​ፈ​ኞች ብዛት የተ​ነሣ ሰዎች ይጮ​ኻሉ፤
ከብ​ዙ​ዎች ክንድ የተ​ነ​ሣም ለር​ዳታ ይጠ​ራሉ።
10ነገር ግን በሌ​ሊት ጥበ​ቃን የሚ​ያ​ዝዝ ፈጣ​ሪዬ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር
ወዴት ነው? የሚል የለም፤
11እር​ሱም ከም​ድር እን​ስ​ሶች ይልቅ፥
ከሰ​ማ​ይም ወፎች ይልቅ የሚ​ለ​የኝ ነው።
12በዚያ ስለ ክፉ ሰዎች ስድብ ይጮ​ኻሉ፥
እርሱ ግን አይ​ሰ​ማ​ቸ​ውም።
13እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ው​ነት ክፉ ነገ​ርን ሊያይ አይ​ወ​ድም።
እርሱ ሁሉን የሚ​ችል ዐዋቂ አም​ላክ ነውና።
14ክፉ የሚ​ሠ​ሩ​ትን አይ​ሰ​ማ​ቸ​ውም፥ እኔ​ንም ያድ​ነ​ኛል፤
አንተ አሁን የሚ​ቻል እንደ መሆኑ መጠን
ልታ​መ​ሰ​ግ​ነው ትችል እንደ ሆነ እስኪ በፊቱ ተዋ​ቀስ።#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
15አሁን ቍጣ​ውን የሚ​ያ​ውቅ የለ​ምና፥
ታላቅ ኀጢ​አ​ቱ​ንም የሚ​ያ​ስብ የለ​ምና።
16ኢዮብ ግን አፉን በከ​ንቱ ይከ​ፍ​ታል፥
ያለ ዕው​ቀ​ትም ቃሉን ያበ​ዛል።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ