ትን​ቢተ ኤር​ም​ያስ 41

41
1እን​ዲ​ህም ሆነ፤ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ከመ​ን​ግ​ሥት ወገ​ንና ከን​ጉሡ ዋና ዋና አለ​ቆች አንዱ የኤ​ሊ​ሳማ ልጅ የና​ታ​ንያ ልጅ እስ​ማ​ኤል ከዐ​ሥር ሰዎች ጋር ወደ መሴፋ ወደ አኪ​ቃም ልጅ ወደ ጎዶ​ል​ያስ መጣ፤ በዚ​ያም በመ​ሴፋ በአ​ንድ ላይ እን​ጀራ በሉ። 2የና​ታ​ን​ያም ልጅ እስ​ማ​ኤል ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በ​ሩት ዐሥሩ ሰዎች ተነ​ሥ​ተው የሳ​ፋ​ንን ልጅ የአ​ኪ​ቃ​ምን ልጅ ጎዶ​ል​ያ​ስን በሰ​ይፍ መቱ፤ የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ በሀ​ገሩ ላይ የሾ​መ​ውን ገደሉ። 3እስ​ማ​ኤ​ልም ከጎ​ዶ​ል​ያስ ጋር በመ​ሴፋ የነ​በ​ሩ​ትን አይ​ሁድ ሁሉ፥ በዚ​ያም የተ​ገ​ኙ​ትን ከለ​ዳ​ው​ያ​ንን ሁሉ፤ ሰል​ፈ​ኞች ሰዎ​ች​ንም#“ሰል​ፈ​ኞች ሰዎ​ች​ንም” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ሁሉ ገደ​ላ​ቸው።
4እስ​ማ​ኤል ማንም ሳያ​ውቅ ጎዶ​ል​ያ​ስን ከገ​ደለ በኋላ በሁ​ለ​ተ​ኛው ቀን እን​ዲህ ሆነ፤ 5ጢማ​ቸ​ውን ላጭ​ተው፥ ልብ​ሳ​ቸ​ው​ንም ቀድ​ደው እያ​ለ​ቀሱ#ዕብ. “ገላ​ቸ​ውን ነጭ​ተው” ሲል ግሪክ ሰባ. ሊ. ደግሞ “ደረ​ታ​ቸ​ውን እየ​ደቁ” የሚል ይጨ​ም​ራል። ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ያቀ​ርቡ ዘንድ የእ​ህል ቍር​ባ​ንና ዕጣን በእ​ጃ​ቸው የያዙ፥ ሰማ​ንያ ሰዎች ከሴ​ኬ​ምና ከሴሎ፥ ከሰ​ማ​ር​ያም መጡ። 6የና​ታ​ን​ያም ልጅ እስ​ማ​ኤል ከመ​ሴፋ ወጥቶ እያ​ለ​ቀሰ ሊገ​ና​ኛ​ቸው ሄደ፤ በተ​ገ​ና​ኛ​ቸ​ውም ጊዜ፥ “ወደ አኪ​ቃም ልጅ ወደ ጎዶ​ል​ያስ ኑ” አላ​ቸው። 7ወደ ከተ​ማም መካ​ከል በመጡ ጊዜ የና​ታ​ንያ ልጅ እስ​ማ​ኤል፥ ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በሩ ሰዎች ገደ​ሉ​አ​ቸው፤ በጕ​ድ​ጓ​ድም መካ​ከል ጣሉ​አ​ቸው። 8በዚ​ያም የተ​ገኙ ዐሥር ሰዎች ቀር​በው እስ​ማ​ኤ​ልን እን​ዲህ አሉት፥ “በሜ​ዳው ድልብ አለ​ንና፥ ገብ​ስና ስንዴ፥ ዘይ​ትና ማርም አለ​ንና አት​ግ​ደ​ለን፤” እር​ሱም በወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው መካ​ከል እነ​ር​ሱን መግ​ደል ተወ።
9እስ​ማ​ኤ​ልም ከጎ​ዶ​ል​ያስ ጋር የገ​ደ​ላ​ቸ​ውን ሰዎች ሬሳ ሁሉ የጣ​ለ​በት ጕድ​ጓድ ንጉሡ አሳ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ንጉሥ ባኦ​ስን ስለ ፈራ የሠ​ራው ጕድ​ጓድ ነበረ፤ የና​ታ​ን​ያም ልጅ እስ​ማ​ኤል የገ​ደ​ላ​ቸ​ውን ሞላ​በት። 10እስ​ማ​ኤ​ልም በመ​ሴፋ የነ​በ​ረ​ውን የሕ​ዝ​ቡን ቅሬታ ሁሉ፥ የን​ጉ​ሡን ሴቶች ልጆች፥ የአ​ዛ​ዦች አለቃ ናቡ​ዛ​ር​ዳን ለአ​ኪ​ቃም ልጅ ለጎ​ዶ​ል​ያስ የሰ​ጠ​ውን በመ​ሴፋ የቀ​ሩ​ትን ሕዝብ ሁሉ መለሰ፤#ዕብ. “ማረ​ካ​ቸው” ይላል። የና​ታ​ን​ያም ልጅ እስ​ማ​ኤል ወደ አሞን ልጆች ይሄድ ዘንድ ተነሣ።
11የቃ​ር​ሔም ልጅ ዮሐ​ናን፥ ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በሩ የጭ​ፍራ አለ​ቆች ሁሉ የና​ታ​ንያ ልጅ እስ​ማ​ኤል ያደ​ረ​ገ​ውን ክፋት ሁሉ ሰሙ። 12ሠራ​ዊ​ቱ​ንም ሁሉ ይዘው ከና​ታ​ንያ ልጅ ከእ​ስ​ማ​ኤል ጋር ሊዋጉ ሄዱ። በገ​ባ​ዖ​ንም ባለው በብዙ ውኃ አጠ​ገብ አገ​ኙት። 13እን​ዲ​ህም ሆነ፤ ከእ​ስ​ማ​ኤል ጋር የነ​በ​ሩት ሕዝብ ሁሉ የቃ​ር​ሔን ልጅ ዮሐ​ና​ንን ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በ​ሩ​ትን የጭ​ፍራ አለ​ቆ​ችን ሁሉ ባዩ ጊዜ ደስ አላ​ቸው። 14እስ​ማ​ኤ​ልም ከመ​ሴፋ የማ​ረ​ካ​ቸው ሕዝብ ሁሉ ተመ​ል​ሰው ወደ ቃር​ሔም ልጅ#“እስ​ማ​ኤ​ልም ከመ​ሴፋ የማ​ረ​ካ​ቸው ሕዝብ ሁሉ ተመ​ል​ሰው ወደ ቃር​ሔም ልጅ” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ወደ ዮሐ​ናን ሔዱ። 15የና​ታ​ንያ ልጅ እስ​ማ​ኤል ግን ከስ​ም​ንት ሰዎች ጋር ከዮ​ሐ​ናን አመ​ለጠ፥ ወደ አሞ​ንም ልጆች ሄደ።
16የቃ​ር​ሔም ልጅ ዮሐ​ናን፥ ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በ​ሩት የጭ​ፍራ አለ​ቆች ሁሉ የአ​ኪ​ቃ​ምን ልጅ ጎዶ​ል​ያ​ስን በመ​ሴፋ ከገ​ደ​ለው በኋላ ከና​ታ​ንያ ልጅ ከእ​ስ​ማ​ኤል ያስ​መ​ለ​ሱ​አ​ቸ​ውን የሕ​ዝ​ቡን ቅሬታ ሁሉ፥ ከገ​ባ​ዖን ያስ​መ​ለ​ሱ​አ​ቸ​ውን ኀያ​ላን ሰል​ፈ​ኞ​ችን፥ ሴቶ​ች​ንም፥ ልጆ​ች​ንም፥ ጃን​ደ​ረ​ቦ​ች​ንም ወሰዱ፤ 17ተነ​ሥ​ተ​ውም ወደ ግብፅ ይሄዱ ዘንድ በቤ​ተ​ል​ሔም አጠ​ገብ በአ​ለው በጌ​ሮት-ከመ​ዓም ተቀ​መጡ፤ 18እስ​ማ​ኤል የባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በሀ​ገሩ ላይ የሾ​መ​ውን የአ​ኪ​ቃ​ምን ልጅ ጎዶ​ል​ያ​ስን ስለ ገደ​ለው ከለ​ዳ​ው​ያ​ንን ፈር​ተ​ዋ​ልና።#ምዕ. 41 በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ምዕ. 48 ነው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ