መጽ​ሐፈ መሳ​ፍ​ንት 15:13-20

መጽ​ሐፈ መሳ​ፍ​ንት 15:13-20 አማ2000

እነ​ር​ሱም፥ “በገ​መድ አስ​ረን በእ​ጃ​ቸው አሳ​ል​ፈን እን​ሰ​ጥ​ሃ​ለን እንጂ አን​ገ​ድ​ል​ህም” ብለው ማሉ​ለት። በሁ​ለ​ትም አዲስ ገመድ አስ​ረው ከዓ​ለቱ ውስጥ አወ​ጡት። የአ​ህያ መን​ጋጋ አጥ​ንት ወደ ተባለ ቦታም ደረሰ፤ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም ደን​ፍ​ተው ተቀ​በ​ሉት፤ ወደ እር​ሱም ሮጡ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መን​ፈስ በእ​ርሱ ላይ አደረ፤ በክ​ን​ዱም ያሉ እነ​ዚያ ገመ​ዶች በእ​ሳት ላይ እንደ ተጣለ ገለባ ሆኑ፤ ማሰ​ሪ​ያ​ውም ከክ​ንዱ ተፈታ፤ የወ​ደቀ የአ​ህያ መን​ጋጋ አጥ​ን​ት​ንም በመ​ን​ገድ አገኘ። እጁ​ንም ዘር​ግቶ ወሰ​ደው፤ በእ​ር​ሱም አንድ ሺህ ሰው ገደለ። ሶም​ሶ​ንም፥ “በአ​ህያ መን​ጋጋ አጥ​ንት ክምር በክ​ምር ላይ አድ​ር​ጌ​አ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በአ​ህያ መን​ጋጋ አጥ​ንት አንድ ሺህ ሰው ገድ​ያ​ለ​ሁና” አለ። መና​ገ​ሩ​ንም በፈ​ጸመ ጊዜ መን​ጋ​ጋ​ውን ከእጁ ጣለ፤ የዚ​ያ​ንም ስፍራ ስም “ቀትለ አጽመ መን​ሰክ” ብሎ ጠራው። እር​ሱም እጅግ ተጠ​ምቶ ነበ​ርና፥ “አንተ ይህ​ችን ታላቅ ማዳን በባ​ሪ​ያህ እጅ ሰጥ​ተ​ሃል፤ አሁ​ንም በጥም እሞ​ታ​ለሁ፤ ባል​ተ​ገ​ረ​ዙ​ትም እጅ እወ​ድ​ቃ​ለሁ” ብሎ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኸ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የዚ​ያ​ችን የአ​ህያ መን​ጋጋ አጥ​ንት ስን​ጥ​ቃት ከፈተ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም ውኃ ወጣ፤ እር​ሱም ጠጣ፤ ነፍ​ሱም ተመ​ለ​ሰች፤ ከውኃ ጥሙም ዐረፈ። ስለ​ዚ​ህም የዚያ ቦታ ስም እስከ ዛሬ ድረስ “ነቅዐ አጽመ መን​ሰክ” ተብሎ ተጠራ። በፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም ዘመን እስ​ራ​ኤ​ልን ሃያ ዓመት ገዛ​ቸው።