መጽሐፈ ኢዮብ 25
25
1ሹሐዊውም በልዳዶስ መለሰ፤ እንዲህም አለ፦
2“ገዢነትና መፈራት በእርሱ ዘንድ ናቸው፥
በከፍታውም#25፥2 በሰማያት። ሰላምን የሚያሰፍን ነው።
3በውኑ ለሠራዊቱ ቍጥር ስፍር አለውን?
ብርሃኑስ የማይወጣው በማን ላይ ነው?
4ሰውስ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፥
ከሴትስ የተወለደ#25፥4 የሰው ልጅ። ንጹሕ ይሆን ዘንድ እንዴት ይችላል?
5እነሆ፥ ጨረቃ እንኳ ብሩህ ካልሆነች፥
ከዋክብትም በፊቱ ንጹሐን ካልሆኑ።
6ይልቁንስ ፈራሽ የሆነ ሰው፥
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ!”
Currently Selected:
መጽሐፈ ኢዮብ 25: መቅካእኤ
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapi.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ