YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 8

8
መዝሙር 8
የፈጣሪ ግርማ በፍጥረቱ ላይ
ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዜም፤ የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤
ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው!
ክብርህ ከሰማያት በላይ፣
ከፍ ከፍ ብሏል።
2ከልጆችና ጡት ከሚጠቡ ሕፃናት አፍ፣
ምስጋናን#8፥2 ወይም ብርታትን አዘጋጀህ፤
ከጠላትህ የተነሣ፣
ባላንጣንና ቂመኛን ጸጥ ታሰኝ ዘንድ።
3የጣቶችህን ሥራ፣
ሰማያትህን ስመለከት፣
በስፍራቸው ያኖርሃቸውን፣
ጨረቃንና ከዋክብትን ሳይ፣
4በዐሳብህ ስፍራ ትሰጠው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?
ትጠነቀቅለትም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድን ነው?
5ከመላእክት በጥቂት አሳነስኸው፤
የክብርንና የሞገስን ዘውድ አቀዳጀኸው።
6በእጆችህ ሥራ ላይ ሾምኸው፤
ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛህለት፤
7በጎችንና ላሞችን ሁሉ፣
የዱር አራዊትንም፣
8የሰማይ ወፎችንና
የባሕር ዓሦችን፣
በባሕር ውስጥ የሚርመሰመሱትንም ሁሉ አስገዛህለት።
9 እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤
ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው!

Currently Selected:

መዝሙር 8: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in