መዝሙር 61
61
መዝሙር 61
ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።
1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴን ስማ፤
ጸሎቴንም አድምጥ።
2ልቤ በዛለ ጊዜ፣
ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጣራለሁ፤
ከእኔ ይልቅ ከፍ ወዳለው ዐለት ምራኝ።
3አንተ መጠጊያዬ፣
ከጠላትም የምተገንብህ ጽኑ ግንብ ሆነኸኛልና።
4በድንኳንህ ለዘላለም ልኑር፤
በክንፎችህም ጥላ ልከለል። ሴላ
5አምላክ ሆይ፤ ስእለቴን ሰምተሃልና፤
ስምህን የሚፈሩትንም ሰዎች ርስት ለእኔ ሰጠህ።
6የንጉሡን ዕድሜ አርዝምለት፤
ዘመኑንም እስከ ብዙ ትውልድ ጨምርለት፤
7በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ይንገሥ፤
ይጠብቁት ዘንድ ምሕረትህንና ታማኝነትህን አዘጋጅለት።
8ስለዚህ ለስምህ ዘወትር ውዳሴ አቀርባለሁ፤
ስእለቴንም በየጊዜው እፈጽማለሁ።
Currently Selected:
መዝሙር 61: NASV
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.