መዝሙር 12
12
መዝሙር 12
ከክፉ ዓለም ለመዳን የቀረበ ጸሎት
ለመዘምራን አለቃ፤ በስምንተኛው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ደግ ሰው የለምና አንተው ድረስልኝ!
ከሰዎችም መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም።
2እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤
በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራሉ።
3ሸንጋዩን ከንፈር ሁሉ፣
ነገር የምታበዛውንም ምላስ እግዚአብሔር ያጥፋ!
4እነዚህም፣ “በአንደበታችን እንረታለን፤
ከንፈራችን የእኛ ነው፤#12፥4 ወይም ከንፈራችን ማረሻ ምላጫችን ነው ጌታችንስ ማነው?”
የሚሉ ናቸው።
5 እግዚአብሔር፣ “ስለ ድኾች መከራ፣
ስለ ችግረኞችም ጩኸት፣
አሁን እነሣለሁ፤
በናፈቁትም ሰላም አኖራቸዋለሁ” ይላል።
6 የእግዚአብሔር ቃል የጠራ ቃል ነው፤
ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ፣
በምድር ላይ በከውር እንደ ተፈተነ ብር ነው።
7 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ትጠብቀናለህ፤
ከዚህም ትውልድ ለዘላለም ትከልለናለህ።
8በሰዎች ዘንድ ክፋት ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ፣
ዐመፀኞች በየአቅጣጫው በዛቻ ይዞራሉ።
Currently Selected:
መዝሙር 12: NASV
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.