ወደ ሮሜ ሰዎች 11:25-36

ወደ ሮሜ ሰዎች 11:25-36 አማ2000

ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን፥ እና ዐዋ​ቂ​ዎች ነን እን​ዳ​ትሉ ይህን ምሥ​ጢር ልታ​ውቁ እወ​ዳ​ለሁ፦ አሕ​ዛብ ሁሉ እስ​ኪ​ገቡ ድረስ ከእ​ስ​ራ​ኤል እኩ​ሌ​ቶ​ችን የልብ ድን​ቍ​ርና አግ​ኝ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና። ከዚህ በኋ​ላም መላው እስ​ራ​ኤል ይድ​ናሉ፤ መጽ​ሐፍ እን​ዲህ እን​ዳለ፥ “አዳኝ ከጽ​ዮን ይወ​ጣል፤ ከያ​ዕ​ቆ​ብም ኀጢ​አ​ትን ያስ​ወ​ግ​ዳል። ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም ባራ​ቅ​ሁ​ላ​ቸው ጊዜ ከእ​ነ​ርሱ ጋር የም​ገ​ባው ኪዳን ይህ ነው።” በወ​ን​ጌል በኩል ስለ እና​ንተ ጠላ​ቶ​ቻ​ችን ናቸው፤ በም​ርጫ በኩል ግን ስለ አባ​ቶች ወዳ​ጆች ናቸው። በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸጋና በመ​ጥ​ራቱ ጸጸት የለ​ምና። ቀድሞ እና​ንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እንደ አል​ታ​ዘ​ዛ​ች​ሁት፥ ዛሬ ግን በእ​ነ​ርሱ አለ​መ​ታ​ዘዝ ይቅር እን​ዳ​ላ​ችሁ፥ እን​ዲ​ሁም እና​ንተ በተ​ማ​ራ​ች​ሁት ምሕ​ረት እነ​ርሱ ምሕ​ረ​ትን እን​ዲ​ያ​ገኙ እነ​ርሱ ዛሬ አል​ታ​ዘ​ዙ​ትም። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሁሉን ይቅር ይለው ዘንድ ሁሉን በኀ​ጢ​አት ውስጥ ዘግ​ቶ​ታ​ልና። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባለ​ጠ​ግ​ነት፥ ጥበ​ብና ዕው​ቀት እን​ዴት ጥልቅ ነው! ለመ​ን​ገ​ዱም ፍለጋ የለ​ውም፤ ፍር​ዱ​ንም የሚ​ያ​ው​ቀው የለም። “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ዐሳ​ቡን ማን ያው​ቃል? ወይስ ማን ተማ​ከ​ረው? ብድ​ሩን ይከ​ፍል ዘንድ ለእ​ርሱ አስ​ቀ​ድሞ ማን አበ​ደ​ረው?” ሁሉ ከእ​ርሱ፥ በእ​ር​ሱና ለእ​ርሱ ነውና፤ ለእ​ር​ሱም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ክብር ምስ​ጋና ይሁን። አሜን።