መዝ​ሙረ ዳዊት 77:10-20

መዝ​ሙረ ዳዊት 77:10-20 አማ2000

የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ኪዳን አል​ጠ​በ​ቁ​ምና፥ በሕ​ጉም ለመ​ሄድ እንቢ አሉ፤ ረድ​ኤ​ቱ​ንና ያሳ​ያ​ቸ​ውን ተአ​ም​ራ​ቱን ረሱ፥ በግ​ብጽ ሀገ​ርና በጣ​ኔ​ዎስ በረሃ በአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ፊት የሠ​ራ​ውን ተአ​ም​ራት። ባሕ​ርን ከፍሎ አሳ​ለ​ፋ​ቸው፤ ውኆ​ችን እንደ ረዋት ውኃ አቆመ። ቀን በደ​መና መራ​ቸው፥ ሌሊ​ቱ​ንም ሁሉ በእ​ሳት ብር​ሃን። ዓለ​ቱን በም​ድረ በዳ ሰነ​ጠቀ፤ ከብዙ ጥልቅ እን​ደ​ሚ​ገኝ ያህል አጠ​ጣ​ቸው። ውኃ​ንም እንደ ወን​ዞች አፈ​ሰሰ። ውኃ​ንም ከዓ​ለት አፈ​ለቀ፥ ነገር ግን እር​ሱን መበ​ደ​ልን እን​ደ​ገና ደገሙ፥ ልዑ​ል​ንም በም​ድረ በዳ አስ​መ​ረ​ሩት። ለነ​ፍ​ሳ​ቸው መብ​ልን ይፈ​ልጉ ዘንድ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በል​ባ​ቸው ፈተ​ኑት። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዲህ ብለው አሙት፦ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድረ በዳ ማዕ​ድን ያሰ​ናዳ ዘንድ ዓለ​ቱን ይመታ ዘንድ ውኃ​ንም ያፈስ ዘንድ ይች​ላ​ልን? እን​ጀ​ራን መስ​ጠ​ትና ለሕ​ዝ​ቡስ ማዕ​ድን መሥ​ራት ይች​ላ​ልን?”