መዝ​ሙረ ዳዊት 121

121
የዳ​ዊት የመ​ዓ​ርግ መዝ​ሙር።
1ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት እን​ሂድ ስላ​ሉኝ ደስ አለኝ።
2ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ፥ እግ​ሮ​ቻ​ችን በአ​ደ​ባ​ባ​ዮ​ችሽ ቆሙ።
3ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምስ እንደ ከተማ የታ​ነ​ጸች ናት።
4እንደ እርሷ ያሉት በአ​ን​ድ​ነት ከእ​ርሷ ጋር ናቸው።
አቤቱ፥ ለስ​ምህ ይገዙ ዘንድ፥
ለእ​ስ​ራ​ኤል ምስ​ክር የሚ​ሆኑ
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወገ​ኖች አሕ​ዛብ ወደ​ዚያ ይወ​ጣ​ሉና።
5ለመ​ፍ​ረድ ዙፋ​ኖ​ቻ​ቸ​ውን በዚያ አስ​ቀ​ም​ጠ​ዋ​ልና፥
የዳ​ዊት ቤት ዙፋ​ኖች።
6የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ደኅ​ን​ነ​ት​ዋን፥ ተነ​ጋ​ገሩ።
ስም​ህን ለሚ​ወ​ድዱ ደስ​ታ​ቸው ነው።
7በኀ​ይ​ልህ ሰላም ይሁን፥
በክ​ብ​ርህ ቦታ ደስታ አለ።
8ስለ ወን​ድ​ሞቼና ስለ ባል​ን​ጀ​ሮቼ ስለ አን​ቺም፥
ሰላ​ምን ይና​ገ​ራሉ።
9ስለ አም​ላኬ ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት
ደኅ​ን​ነ​ት​ሽን ፈለ​ግሁ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ