መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 1

1
1የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከግ​ብፅ በወ​ጡ​በት በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዘመን እን​ዲህ ሆነ። በሦ​ስ​ተ​ኛው ወር፥ ያ ወር በባተ በዐ​ሥራ ስድ​ስ​ተ​ኛው ቀን፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፥ “ከእኔ ዘንድ ወደ​ዚህ ተራራ ውጣ፤ በጻ​ፍ​ኸ​ውም መጠን ልብ ታስ​ደ​ር​ጋ​ቸው ዘንድ ሕጉና ሥር​ዐቱ የተ​ጻ​ፉ​ባ​ቸ​ውን ሁለ​ቱን የዕ​ንቍ ጽላት እሰ​ጥ​ሀ​ለሁ” ብሎ ለሙሴ ተና​ገረ። 2ሙሴም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተራራ ወጣ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ብር​ሃን በደ​ብረ ሲና ተገ​ለጠ። ስድ​ስት ቀንም ደመና ጋረ​ደው። 3በሰ​ባ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በደ​መና መካ​ከል ሆኖ ሙሴን ጠራው፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ብር​ሃን በተ​ራ​ራው ራስ ላይ እንደ እሳት ሲነ​ድድ አየ።
4ሙሴም በተ​ራ​ራው ላይ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ተቀ​መጠ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያለ​ፈ​ው​ንና የሚ​መ​ጣ​ውን፥ ሕጉ የሚ​ጠ​በ​ቅ​በ​ት​ንና አም​ል​ኮቱ የሚ​ነ​ገ​ር​በ​ትን፥ የዘ​መ​ኑን ሁሉ አከ​ፋ​ፈል ነገር አመ​ለ​ከ​ተው። 5እን​ዲ​ህም አለው፥ “በዚህ ተራራ ላይ እኔ በም​ነ​ግ​ርህ ነገር ሁሉ ልብ​ህን አኑር። በአ​ን​ተና በእኔ መካ​ከል በደ​ብረ ሲና ዛሬ ለል​ጆ​ቻ​ቸው የሚ​ደ​ረ​ገ​ውን፥ እኔ የም​ሠ​ራ​ውን ሥር​ዐት ለማ​ስ​ፈ​ረስ ስለ ሠሩት ኀጢ​አት ሁሉ እንደ ተለ​የ​ሁ​አ​ቸው ልጆ​ቻ​ቸው ይሰሙ ዘንድ በመ​ጽ​ሐፍ ጻፈው።” 6ይህ ሁሉ ነገር በእ​ነ​ርሱ ላይ በመ​ጣ​ባ​ቸው ጊዜ እን​ዲህ ይና​ገ​ራል። በፈ​ረ​ድ​ሁ​ባ​ቸው ሁሉ፥ በሥ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ ከእ​ነ​ርሱ ይልቅ እኔ እው​ነ​ተኛ እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ያለሁ እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ። 7አን​ተም እኔ ዛሬ የነ​ገ​ር​ሁ​ህን ይህን ሁሉ ነገር ጻፍ። እኔ ቍጣ​ቸ​ውን አው​ቃ​ለ​ሁና፥ ማርና ወተ​ትን የም​ታ​ስ​ገኝ ሀገ​ርን ለል​ጆ​ቻ​ችሁ እሰ​ጣ​ለሁ ብዬ ለአ​ብ​ር​ሃ​ምና ለይ​ስ​ሐቅ ለያ​ዕ​ቆ​ብም ወደ​ማ​ል​ሁ​ላ​ቸው ሀገር ሳላ​ገ​ባ​ቸው አን​ገ​ታ​ቸው ደን​ዳና እንደ ሆነ አው​ቃ​ለ​ሁና፥ በል​ተ​ውና ጠግ​በው ከመ​ከ​ራ​ቸው ሁሉ ወደ​ማ​ያ​ድ​ና​ቸው ወደ ልዩ ጣዖት ይመ​ለ​ሳ​ሉና። 8ይህች መጽ​ሐፍ በእ​ነ​ርሱ ላይ ሥር​ዐት ትሁ​ን​ባ​ቸው። እኔ የማ​ዝ​ዛ​ቸ​ውን ትእ​ዛ​ዜን ሁሉ ይዘ​ነ​ጋ​ሉና፥ አሕ​ዛ​ብ​ንም ተከ​ት​ለው ወደ ኀጢ​አ​ታ​ቸው ይሄ​ዳ​ሉና፥ ለጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ይገ​ዛ​ሉና፤ በእ​ነ​ር​ሱም መከ​ራ​ንና ጭን​ቅን፥ ጦር​ንም ለማ​ም​ጣት መሰ​ና​ክል ይሆ​ን​ባ​ቸ​ዋል።
9“ብዙ ሰዎች ይጠ​ፋሉ፥ ተይ​ዘ​ውም በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው እጅ ይወ​ድ​ቃሉ። ሥር​ዐ​ቴ​ንና ትእ​ዛ​ዜን፥ የቃል ኪዳ​ኔ​ንም በዓ​ላት፥ ሰን​በ​ታ​ት​ንም፥ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም የለ​የ​ሁ​ትን ቅድ​ሳ​ቴን፤ ስሜ በእ​ርሱ ይጠራ ዘንድ፥ ያድ​ር​በ​ትም ዘንድ በም​ድር መካ​ከል ያከ​በ​ር​ሁ​ትን ድን​ኳ​ኔ​ንና መቅ​ደ​ሴን ትተ​ዋ​ልና። 10በዓ​ላ​ትን፥ መስ​ገጃ ዛፍ​ንና ጣዖ​ትን ሠር​ተው ለመ​ሳት እየ​ራ​ሳ​ቸው ይሰ​ግ​ዳሉ። ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለአ​ጋ​ን​ንት፥ በል​ቡ​ና​ቸው ስተው ለሠ​ሩ​ትም ጣዖት ሁሉ ይሠ​ዋሉ፤ አዳ​ኝ​ባ​ቸ​ውም ዘንድ ወደ እነ​ርሱ ምስ​ክ​ሮ​ችን እል​ካ​ለሁ። ነገር ግን አይ​ሰ​ሙም፤ ምስ​ክ​ሮ​ች​ንም ይገ​ድ​ላሉ። 11ሕግን የሚሹ ሰዎ​ች​ንም ይገ​ድ​ሉ​አ​ቸ​ዋል፤ ከሀ​ገ​ርም አስ​ወ​ጥ​ተው ይሰ​ድ​ዱ​አ​ቸ​ዋል፤ ሁሉ​ንም ያቦ​ዝ​ናሉ፤ በዐ​ይ​ኖ​ችም ፊት ክፉ ሥራ መሥ​ራ​ትን ይጀ​ም​ራሉ። 12ከእ​ነ​ር​ሱም ፊቴን እመ​ል​ሳ​ለሁ፤ ለመ​በ​ዝ​በ​ዝና ለመ​ማ​ረክ፥ ለመ​ዘ​ረ​ፍም ይሆኑ ዘንድ በአ​ሕ​ዛብ እጅ አሳ​ልፌ እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም መካ​ከል አር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በአ​ሕ​ዛ​ብም መካ​ከል እበ​ት​ና​ቸ​ዋ​ለሁ።
13“ሕጌን ሁሉ፥ ትእ​ዛ​ዜ​ንም ሁሉ፥ ፍር​ዴ​ንም ሁሉ፥ ሥር​ዐ​ቴ​ንም ሁሉ ይዘ​ነ​ጋሉ። የወ​ሩን መባ​ቻና ሰን​በ​ትን፥ በዓ​ሉ​ንና ኢዮ​ቤ​ል​ዩን፥ ሥር​ዐ​ቱ​ንም፥ ይዘ​ነ​ጋሉ። 14ከዚ​ህም በኋላ በፍ​ጹም ልባ​ቸው፥ በፍ​ጹም ነፍ​ሳ​ቸው፥ በፍ​ጹም ኀይ​ላ​ቸ​ውም ከአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ወደ እኔ ይመ​ለ​ሳሉ። እኔም ከአ​ሕ​ዛብ ሁሉ መካ​ከል እሰ​በ​ስ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ። 15እገ​ለ​ጥ​ላ​ቸው ዘንድ ይፈ​ል​ጉ​ኛል። በፍ​ጹም ልባ​ቸ​ውና በፍ​ጹም ነፍ​ሳ​ቸ​ውም በፈ​ለ​ጉኝ ጊዜ፥ እኔ በእ​ው​ነት ብዙ ሰላ​ምን እገ​ል​ጥ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በፍ​ጹም ልቤና በፍ​ጹም ነፍሴ ወደ ቀና ሕግ እመ​ል​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ። 16ለበ​ረ​ከት ይሆ​ናሉ፤ ለመ​ር​ገ​ምም አይ​ደ​ለም፤ ራስ ይሆ​ናሉ፤ ጅራ​ት​ንም አይ​ደ​ለም፤ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም መቅ​ደ​ሴን እሠ​ራ​ለሁ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር እኖ​ራ​ለሁ፤ አም​ላ​ካ​ቸ​ውም እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም በሚ​ገባ በእ​ው​ነት ሕዝቤ ይሆ​ናሉ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ቸው ነኝና አል​ተ​ዋ​ቸ​ውም፤ አል​ለ​ያ​ቸ​ው​ምም።”
17ሙሴም በግ​ን​ባሩ ተደ​ፍቶ ጸለየ፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “አቤቱ፥ አም​ላኬ፥ በል​ቡ​ና​ቸው ስሕ​ተት ይሄዱ ዘንድ ርስ​ትህ የሆኑ ወገ​ኖ​ች​ህን አት​ተው። ይገ​ዙ​አ​ቸ​ውም ዘንድ፥ አን​ተ​ንም እን​ዲ​በ​ድሉ ያደ​ር​ጓ​ቸው ዘንድ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው በአ​ሕ​ዛብ እጅ አት​ጣ​ላ​ቸው። 18አቤቱ፥ ይቅ​ር​ታህ በወ​ገ​ኖ​ችህ ላይ ከፍ ከፍ ይበል፤ የቀና ልቡ​ና​ንም ፍጠ​ር​ላ​ቸው። በፊ​ትህ ለማ​ጣ​ላት ፥ ከባ​ለ​ም​ዋ​ል​ነ​ት​ህም ይጠፉ ዘንድ ከእ​ው​ነ​ተኛ ሥራ ሁሉ ለማ​ሰ​ነ​ካ​ከል የዲ​ያ​ብ​ሎስ መን​ፈስ አይ​ሠ​ል​ጥ​ን​ባ​ቸው። 19እነ​ር​ሱስ በታ​ላቅ ኀይ​ልህ ከግ​ብፅ ሰዎች እጅ ያዳ​ን​ኻ​ቸው ወገ​ኖ​ች​ህና ማደ​ሪ​ያ​ዎ​ችህ ናቸው። ንጹሕ ልቡ​ናን ፍጠ​ር​ላ​ቸው። የተ​ቀ​ደሰ መን​ፈ​ስ​ንም አሳ​ድ​ር​ባ​ቸው፤ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው አይ​ሰ​ነ​ካ​ከሉ።”
20እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን እን​ዲህ አለው፥ “እኔ ክር​ክ​ራ​ቸ​ው​ንና አሳ​ባ​ቸ​ውን አው​ቃ​ለሁ፤ አን​ገ​ታ​ቸው ደን​ዳና ነው። ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንና የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ኀጢ​አት እስ​ኪ​ያ​ውቁ ድረስ አይ​ሰ​ሙም። 21ከዚ​ህም በኋላ በፍ​ጹም ቅን​ነት፥ በፍ​ጹም ልቡ​ናና በፍ​ጹም ሰው​ነት ወደ እኔ ይመ​ለ​ሳሉ። የል​ቡ​ና​ቸ​ውን ቈላ​ፍ​ነ​ትና የዘ​ራ​ቸ​ውን ልቡና ቈላ​ፍ​ነት እቈ​ር​ጣ​ለሁ። ንጹሕ ልቡ​ና​ንም እፈ​ጥ​ር​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ። 22ከዚ​ያች ቀን ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ እኔን ከመ​ከ​ተል ወደ ኋላ እን​ዳ​ይ​መ​ለሱ አነ​ጻ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ልቡ​ና​ቸ​ውም እኔን ትከ​ተ​ላ​ለች፤ ትእ​ዛ​ዜ​ንም ሁሉ ይፈ​ጽ​ማሉ። 23አባት እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም ልጆች ይሆ​ኑ​ኛል፤ ሁሉም የሕ​ያው አም​ላክ ልጆች ይባ​ላሉ። መል​አክ ሁሉ፥ ሰውም ሁሉ ያው​ቃ​ቸ​ዋል። እነ​ርሱ ልጆች እንደ ሆኑ፥ እኔም በሚ​ገ​ባና በእ​ው​ነት አባ​ታ​ቸው እንደ ሆንሁ፥ እን​ደ​ም​ወ​ድ​ዳ​ቸ​ውም ያው​ቋ​ቸ​ዋል። 24አን​ተም በዚህ ተራራ ላይ እኔ የም​ነ​ግ​ር​ህን ይህን ነገር ሁሉ፥ የፊ​ቱ​ንና የኋ​ላ​ውን፥ ይመጣ ዘንድ ያለ​ው​ንም፥ ሕጉና አም​ል​ኮ​ቱም በሚ​ነ​ገ​ሩ​በት በዓ​መቱ ቍጥር እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ የሚ​ሆ​ነ​ውን የዘ​መ​ኑን አከ​ፋ​ፈል ሁሉ፥ እኔም ወርጄ በዘ​መኑ ሁሉ ከእ​ነ​ርሱ ጋር እስ​ክ​ኖር ድረስ የሚ​ደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ ጻፍ።”
25መል​አከ ገጹ​ንም እን​ዲህ አለው፥ “ዓለም ከተ​ፈ​ጠረ ጀምሮ ለዘ​ለ​ዓ​ለም የም​መ​ሰ​ገ​ን​በት ቤተ መቅ​ደስ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው እስ​ኪ​ሠራ ድረስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለሁሉ እስ​ኪ​ታይ ድረስ የሚ​ሆ​ነ​ውን ለሙሴ ጻፍ​ለት። 26እኔ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እንደ ሆንሁ፥ ለያ​ዕ​ቆብ ልጆች ሁሉ አባት እንደ ሆንሁ፤ በደ​ብረ ጽዮ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ንጉሥ እንደ ሆንሁ ሁሉ ያው​ቃል፤ ጽዮን ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም የከ​በ​ረች ትሆ​ና​ለች።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ