መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 2

2
1በእ​ስ​ራ​ኤል ሠራ​ዊት ፊት የሚ​ሄድ መል​አከ ገጹም የዘ​መ​ኖች አከ​ፋ​ፈል የተ​ጻ​ፈ​በ​ትን ጽላት ያዘ። 2ይኸ​ውም ለሕ​ግና ለም​ስ​ክ​ር​ነት በሱ​ባዔ የሚ​ቈ​ጠ​ረው የዘ​መኑ አከ​ፋ​ፈል ከዓ​ለም ፍጥ​ረ​ትና አዲስ ፍጥ​ረት ከተ​ፈ​ጠ​ረ​በት ቀን ጀምሮ፥ ሰማ​ያ​ትና ምድር፥ ፍጥ​ረ​ታ​ቸ​ውም ሁሉ የሰ​ማይ ሠራ​ዊት እንደ መሆ​ና​ቸው እስ​ኪ​ታ​ደሱ ድረስ ያለው የተ​ጻ​ፈ​በት ነው። 3የም​ድር ፍጥ​ረት ሁሉ እንደ መሆ​ና​ቸ​ውም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መቅ​ደስ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና በደ​ብረ ጽዮን እስ​ኪ​ሠራ ድረስ፥ ብር​ሃ​ና​ትም ሁሉ ከእ​ስ​ራ​ኤል ለተ​መ​ረጡ ሰዎች ሁሉ ለደ​ኅ​ን​ነት፥ ለሰ​ላ​ምና ለበ​ረ​ከት ሊሆኑ እስ​ኪ​ታ​ደሱ ድረስ፥ ከዚ​ህች ቀን ጀምሮ እስከ ምድር ዘመን ሁሉ እን​ደ​ዚሁ ይሆን ዘንድ የሚ​ደ​ረ​ገው ሁሉ የተ​ጻ​ፈ​በት ነው።
4መል​አከ ገጹም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ሙሴን እን​ዲህ አለው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላክ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ቀን ፍጥ​ረ​ቱን ሁሉ ፈጥሮ እንደ ጨረሰ፥ የፍ​ጥ​ረ​ትን ነገር ሁሉ ጻፍ፤ 5በሰ​ባ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን እን​ዳ​ረፈ፥ ከዕ​ለ​ታ​ቱም ሁሉ እንደ ለያት፥ ለሥ​ራ​ውም ሁሉ ምል​ክት አድ​ርጎ እን​ዳ​ኖ​ራት ጻፍ። በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ቀን በላይ ያሉ ሰማ​ዮ​ችን ፈጥ​ሮ​አ​ልና፤ ምድ​ር​ንና ውኃ​ዎ​ች​ንም፥ በፊቱ የሚ​ያ​ገ​ለ​ግል ፍጥ​ረ​ት​ንም ሁሉ ፈጥ​ሮ​አ​ልና። 6መላ​እ​ክተ ገጽ​ንም፥ የሚ​ያ​መ​ሰ​ግኑ መላ​እ​ክ​ት​ንም፥ በእ​ሳት አካል ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ት​ንም፥ በነ​ፋስ አካል ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ትን፥ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ አካል ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ት​ንም፥ በበ​ረ​ድና በው​ርጭ አካል ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ት​ንም፥ 7በውኃ ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ትን፥ በነ​ጐ​ድ​ጓ​ድና በመ​ብ​ረቅ ላይ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ትን፥ በቍ​ርና በው​ርጭ፥ በክ​ረ​ም​ትና በመ​ጸው፥ በጸ​ደ​ይና በበጋ፥ በሰ​ማ​ይና በም​ድር ባሉ ነፋ​ሳት ሁሉ የተ​ሾሙ መላ​እ​ክ​ትን፥ በወ​ንዙ ሁሉ፥ በጨ​ለ​ማና በብ​ር​ሃን፥ በን​ጋ​ትና በም​ሽት በባ​ሕ​ርይ ዕው​ቀቱ ባዘ​ጋ​ጃ​ቸው ላይ የተ​ሾሙ መለ​እ​ክ​ትን ፈጥ​ሮ​አ​ልና።” 8ያን​ጊ​ዜም ሥራ​ውን አይ​ተን ስለ ሠራው ሥራ ሁሉ በፊቱ ፈጽ​መን አመ​ሰ​ገ​ን​ነው፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ቀን ሰባት ታላ​ላቅ ሥራ​ዎ​ችን ሠር​ቶ​አ​ልና።
9በሁ​ለ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በሐ​ኖ​ስና በው​ቅ​ያ​ኖስ መካ​ከል ጠፈ​ርን አድ​ር​ጎ​አ​ልና፤ በዚ​ያ​ችም ቀን ውኃ​ዎች ተከ​ፍ​ለው እኩ​ሌ​ቶቹ ወደ ላይ ወጥ​ተ​ዋ​ልና፤ እኵ​ሌ​ቶቹ ከጠ​ፈር በታች ወዳ​ለው ወደ ምድር መካ​ከል ወር​ደ​ዋ​ልና፤ በሁ​ለ​ተ​ኛው ቀን ይህን ሥራ ብቻ ሠራ።
10በሦ​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን፥ “ውኃ​ዎች ከም​ድር ላይ ወደ አንዱ ቦታ ሄደው ይወ​ሰኑ፥ ምድ​ርም ትገ​ለጥ” ብሎ እንደ ተና​ገ​ረው አድ​ር​ጎ​አ​ልና። 11ውኃ​ዎ​ችም እን​ዳ​ዘ​ዛ​ቸው እን​ደ​ዚሁ ተዘ​ጋጁ። ከም​ድር ፊት ወደ አንድ ቦታ ሄደው ከዚህ ከጠ​ፈር በታች በው​ቅ​ያ​ኖስ ተወ​ሰኑ፤ ምድ​ርም ተገ​ለ​ጠች። 12በዚ​ያ​ችም ቀን በየ​መ​ወ​ሰ​ኛ​ቸው የባ​ሕር ጥል​ቆ​ችን ፈጠ​ረ​ላት፤ ፈሳ​ሾ​ች​ንም ሁሉ፥ የው​ኃ​ዎ​ች​ንም መወ​ሰ​ኛ​ዎች፥ በተ​ራ​ራ​ዎች ሥር በም​ድር ውስጥ ምን​ጮች ሁሉና በተ​ራ​ራ​ዎች ሥር ያሉ የው​ኃ​ዎ​ችን መወ​ሰ​ኛ​ዎች ሁሉ፥ በም​ድር ያሉ የው​ኃ​ዎ​ች​ንም ጕድ​ጓድ ሁሉ ፈጠ​ረ​ላት። በየ​ዘ​ሩም የሚ​ዘ​ራ​ውን ዘር፥ የሚ​በ​ላ​ው​ንም ዘር ሁሉ፥ የሚ​ያ​ፈሩ እን​ጨ​ቶ​ች​ንና ዛፎ​ች​ንም፥ በገ​ነ​ትም ለተ​ድላ የተ​ፈ​ጠሩ ተክ​ሎ​ችን፥ በሦ​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን እነ​ዚ​ህን አራ​ቱን ታላ​ላ​ቆች ፍጥ​ረ​ቶች ፈጠረ።
13በአ​ራ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን ጨረ​ቃ​ንና ፀሓ​ይን፥ ከዋ​ክ​ብ​ት​ንም ፈጥሮ በዓ​ለሙ ሁሉ ያበሩ ዘንድ በጠ​ፈር አኖ​ራ​ቸው። ሌሊ​ት​ንና ቀን​ንም አስ​ገ​ዛ​ቸው፤ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ መካ​ከ​ልም ለመ​ለ​የት ድን​በር አደ​ረ​ጋ​ቸው። 14እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በም​ድር ላይ ለቀ​ኖ​ችና ለሱ​ባ​ዔ​ዎች፥ ለወ​ሮ​ችና ለበ​ዓ​ሎች፥ ለዓ​መ​ታ​ትና ለኢ​ዮ​ቤ​ላት፥ በዓ​መት ለሚ​መ​ላ​ለሱ ሰዓ​ቶ​ችም ሁሉ ታላቅ ምል​ክት እን​ዲ​ሆን፥ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ መካ​ከ​ልም ድን​በ​ርን እን​ዲ​ለይ፥ በም​ድ​ርም ላይ የሚ​በ​ቅ​ለ​ውና የሚ​ያ​ድ​ገው ሁሉ ይድን ዘንድ፥ ለማ​ዳን ፀሐ​ይን ፈጠረ፤ በአ​ራ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን እነ​ዚ​ህን ሦስ​ቱን ፍጥ​ረ​ቶች ፈጥረ።
15በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በጥ​ልቅ ውኃ​ዎች መካ​ከል ያሉ​ትን ታላ​ላቅ ዓሣ አን​በ​ሪ​ዎች ፈጠረ። ይህ ሁሉ መጀ​መ​ሪያ በእጁ ተፈ​ጥ​ሮ​አ​ልና፤ ሥጋዊ ደማዊ ሁሉ፥ በው​ኃ​ዎ​ችም ውስጥ የሚ​መ​ላ​ለስ ፍጥ​ረት ሁሉ፥ ዓሣ​ዎ​ችና የሚ​በሩ ወፎች ሁሉ፥ ወገ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም ሁሉ ተፈ​ጥ​ረ​ዋ​ልና፤ 16ፀሓ​ይም ሕይ​ወት ሊሆ​ና​ቸው በእ​ነ​ርሱ ላይ ወጥ​ቶ​አ​ልና፥ በዚህ ዓለም በሚ​ኖር ፍጥ​ረ​ትና በም​ድር በሚ​በ​ቅ​ለው ሁሉ ላይ፥ በሚ​ያ​ፈ​ራ​ውም እን​ጨት ሁሉ ላይ፥ በሥ​ጋዊ ደማዊ ሁሉ ላይ ወጥ​ቶ​አ​ልና፤ በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን እነ​ዚ​ህን ሦስ​ቱን ፍጥ​ረ​ታት ሁሉ ፈጠረ።
17በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን እን​ስ​ሳ​ት​ንና አራ​ዊ​ትን ሁሉ በም​ድር ላይ የሚ​መ​ላ​ለ​ሰ​ው​ንም ፍጥ​ረት ሁሉ ፈጠረ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ