የYouVersion አርማ
የፍለጋ አዶ

መጽ​ሐፈ ኢዮብ 38

38
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለኢ​ዮብ እንደ መለ​ሰ​ለት
1ኤል​ዩስ ንግ​ግ​ሩን ካቆመ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በደ​መ​ናና በዐ​ውሎ ነፋስ ውስጥ ሆኖ ኢዮ​ብን ጠየ​ቀው፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ተና​ገ​ረው” ይላል። እን​ዲ​ህም አለው፦
2“ከእኔ ምክ​ርን የሚ​ሸ​ሽግ፥
በል​ቡም ነገ​ርን የሚ​ደ​ብቅ ማን ነው?
ከእኔ ይሰ​ው​ረ​ዋ​ልን?
3እን​ግ​ዲህ እንደ ሰው ወገ​ብ​ህን ታጠቅ፤
እጠ​ይ​ቅ​ሃ​ለሁ፥ አን​ተም መል​ስ​ልኝ።
4ምድ​ርን በመ​ሠ​ረ​ትሁ ጊዜ አንተ ወዴት ነበ​ርህ?
ታስ​ተ​ውል እንደ ሆነ ንገ​ረኝ።
5ብታ​ውቅ መስ​ፈ​ሪ​ያ​ዋን የወ​ሰነ፥
በላ​ይ​ዋስ የመ​ለ​ኪያ ገመ​ድን የዘ​ረጋ ማን ነው?
6መሠ​ረ​ቶ​ችዋ በምን ላይ ተተ​ክ​ለው ነበር?
የማ​ዕ​ዘ​ን​ዋ​ንስ ድን​ጋይ ያቆመ ማን ነው?
7ከዋ​ክ​ብት በተ​ፈ​ጠሩ ጊዜ
መላ​እ​ክቴ ሁሉ በታ​ላቅ ድምፅ አመ​ሰ​ገ​ኑኝ#ዕብ. “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ልጆች” ይላል።
8ከእ​ናቷ ማኅ​ፀን በወ​ጣች ጊዜ፥
ባሕ​ርን በመ​ዝ​ጊ​ያ​ዎች ዘጋ​ኋት፤
9ደመ​ና​ውን ልብስ አደ​ረ​ግ​ሁ​ላት።
በጭ​ጋ​ግም ጠቀ​ለ​ል​ኋት።
10ድን​በ​ርም አደ​ረ​ግ​ሁ​ላት።
መወ​ር​ወ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ንና መዝ​ጊ​ያ​ዎ​ች​ንም አኖ​ርሁ።
11እስ​ከ​ዚህ ድረስ ድረሺ፥ ከወ​ሰ​ን​ሽም አት​ለፊ፤
ነገር ግን ማዕ​በ​ልሽ በመ​ካ​ከ​ልሽ ይገ​ደብ አል​ኋት።
12“የን​ጋት ወገ​ግታ በአ​ንተ ተፈ​ጥ​ሮ​አ​ልን?
የአ​ጥ​ቢያ ኮከ​ብስ ትእ​ዛ​ዙን በአ​ንተ ዐው​ቋ​ልን?
13የም​ድ​ርን ዳርቻ ይይዝ ዘንድ፥
ከእ​ር​ስ​ዋም ኃጥ​ኣ​ንን ያና​ውጥ ዘንድ።
14አንተ ጭቃ​ውን ከመ​ሬት ወስ​ደህ
ሕያው ፍጥ​ረ​ትን ፈጥ​ረ​ሃ​ልን?
በም​ድ​ርስ ላይ እን​ዲ​ና​ገር አድ​ር​ገ​ሃ​ልን?
15የኃ​ጥ​ኣ​ንን ብር​ሃ​ና​ቸ​ውን ከል​ክ​ለ​ሃ​ልን?
የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ች​ንስ ክንድ ሰብ​ረ​ሃ​ልን?
16ወደ ባሕር ምን​ጭስ ውስጥ ገብ​ተ​ሃ​ልን?
በጥ​ል​ቁስ መሠ​ረት ውስጥ ተመ​ላ​ል​ሰ​ሃ​ልን
17ከግ​ር​ማ​ህስ የተ​ነሣ የሞት በሮች ተከ​ፍ​ተ​ው​ል​ሃ​ልን?
የሲ​ኦል በረ​ኞ​ችስ አን​ተን አይ​ተው ይደ​ነ​ግ​ጣ​ሉን?
18ከሰ​ማይ በታች ያለ የም​ድ​ር​ንስ ስፋት አስ​ተ​ው​ለ​ሃ​ልን?
መጠ​ኑም ምን ያህል እንደ ሆነ እስኪ ንገ​ረኝ!
19“የብ​ር​ሃን ማደ​ር​ያው ቦታ የት ነው?
የጨ​ለ​ማስ ቦታው ወዴት አለ?
20ትችል እንደ ሆነ፥
መን​ገ​ዳ​ቸ​ው​ንም ታውቅ እን​ደ​ሆነ፥
ወደ ዳር​ቻ​ቸው እስኪ ውሰ​ደኝ።
21በዚ​ያን ጊዜ ተወ​ል​ደህ ነበ​ርና፥
የዕ​ድ​ሜ​ህም ቍጥር ብዙ ነውና፥
በእ​ው​ነት አንተ ሳታ​ውቅ አት​ቀ​ርም።
22በውኑ ወደ በረ​ዶው ቤተ መዛ​ግ​ብት ገብ​ተ​ሃ​ልን?
የበ​ረ​ዶ​ው​ንስ ቅን​ጣት ቤተ መዛ​ግ​ብት አይ​ተ​ሃ​ልን?
23ይህስ በጠ​ላ​ትህ ጊዜ
ለሰ​ል​ፍና ለጦ​ር​ነት ቀን ይጠ​በ​ቅ​ል​ሃ​ልን?
24አመ​ዳይ ከየት ይወ​ጣል?
ከሰ​ማይ በታች ያለ የአ​ዜብ ነፋ​ስስ እን​ዴት ይበ​ተ​ናል?
25ለኀ​ይ​ለ​ኛው ዝናብ መው​ረ​ጃ​ውን፥
ወይስ ለሚ​ያ​ን​ጐ​ዳ​ጕ​ደው መብ​ረቅ መን​ገ​ድን ያዘ​ጋጀ ማን​ነው?
26ማንም በሌ​ለ​በት ምድር ላይ፥
ሰውም በማ​ይ​ኖ​ር​በት ምድረ በዳ ይዘ​ንም ዘንድ፥
27ባድ​ማ​ው​ንና ውድ​ማ​ውን ያጠ​ግብ ዘንድ፥
ሣሩ​ንም በም​ድረ በዳ ያበ​ቅል ዘንድ፥
28የዝ​ናብ አባቱ ማን ነው?
ወይስ የጠ​ልን ነጠ​ብ​ጣብ የወ​ለደ ማን ነው?
29በረ​ዶስ ከማን ማኅ​ፀን ይወ​ጣል?
የሰ​ማ​ዩ​ንስ አመ​ዳይ ማን ወለ​ደው?
30እር​ሱም እንደ ፈሳሽ ውኃ ይወ​ር​ዳል።
ውኆች እንደ ድን​ጋይ ጠነ​ከሩ፥
የኃ​ጥ​ኣ​ን​ንስ ፊት ማን አዋ​ረደ?#ዕብ. “የቀ​ላ​ዩም ፊት ረግ​ት​ዋል” ይላል።
31“በውኑ የሰ​ባ​ቱን ከዋ​ክ​ብት#በግ​እዝ “ትርያ” በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. “ፕሊ​አዛ” ይላል። ዘለላ ታስር ዘንድ፥
ወይስ ኦሪ​ዮን#ግእዙ “ደብ​ራን” ይላል። የሚ​ባ​ለ​ውን ኮከብ ትፈታ ዘንድ ትች​ላ​ለ​ህን?
32ወይስ ማዛ​ሮት#በግ​እዝ “ብል​አ​ተ​ናሽ” ይላል። የሚ​ባ​ሉ​ትን ከዋ​ክ​ብት በጊ​ዜ​ያ​ቸው ታወጣ ዘንድ፥
ወይስ የም​ሽ​ቱን ኮከብ ከል​ጆቹ ጋር ትመራ ዘንድ ትች​ላ​ለ​ህን?
33የሰ​ማ​ይን ሥር​ዐት፥
ከሰ​ማይ በታ​ችስ የሚ​ሆ​ነ​ውን ታው​ቃ​ለ​ህን?
34ደመ​ና​ውን በቃ​ልህ ትጠ​ራ​ዋ​ለ​ህን?
ብዙ ውኃስ እየ​ተ​ን​ቀ​ጠ​ቀጠ ይመ​ል​ስ​ል​ሃ​ልን?
35መብ​ረ​ቁን ትል​ከ​ዋ​ለ​ህን? እር​ሱስ ይሄ​ዳ​ልን?
ደስ​ታ​ህስ ምን​ድን ነው ይል​ሃ​ልን?
36ለሴ​ቶች የፈ​ት​ልን ጥበ​ብና
የተ​ለ​ያዩ የጥ​ልፍ ሥራ​ዎ​ችን ዕው​ቀት ማን ሰጠ?
37የሰ​ማ​ይን ደመና በጥ​በቡ ሊቈ​ጥር የሚ​ችል ማን ነው?
ሰማ​ይ​ንም ወደ ምድር ያዘ​ነ​በለ ማን ነው?
38እንደ ትቢያ በም​ድር ተዘ​ር​ግቷል፤
እንደ ዓለት ድን​ጋ​ይም አጣ​በ​ቅ​ሁት።
39“ለአ​ን​በ​ሳ​ዪቱ አደን ታድ​ና​ለ​ህን?
የእ​ባ​ቦ​ች​ንስ ነፍስ ታጠ​ግ​ባ​ለ​ህን?
40በዋ​ሾ​ቻ​ቸው ውስጥ ተጋ​ድ​መው
በጫ​ካም ውስጥ አድ​ብ​ተው ይቀ​መ​ጣ​ሉና።
41ልጆቹ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሲጮኹ፥
የሚ​በ​ሉ​ትም ፈል​ገው ሲቅ​በ​ዘ​በዙ፥
ለቍራ መብ​ልን የሚ​ሰ​ጠው ማን ነው?

ማድመቅ

Share

Copy

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ