የYouVersion አርማ
የፍለጋ አዶ

መጽ​ሐፈ ኢዮብ 36

36
የኤ​ል​ዩስ መጨ​ረሻ ንግ​ግር
1ኤል​ዩ​ስም ደግሞ መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“ገና የም​ና​ገ​ረው ነገር አለ​ኝና ጥቂት ታገ​ሠኝ፥
እኔም አስ​ተ​ም​ር​ሃ​ለሁ።
3ዕው​ቀ​ቴን ከሩቅ አመ​ጣ​ለሁ፥
ሥራ​ዬ​ንም እው​ነት ነው እላ​ለሁ።
4ቃሌ ሐሰት ያይ​ደለ እው​ነት ነው።
አን​ተም የዐ​መፅ ቃላ​ትን አት​ሰ​ማም።
5“በጥ​በብ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ጥበብ” ይላል። ብር​ቱና ኀያል የሆነ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፥
የዋ​ሁን ሰው እን​ደ​ማ​ይ​ጥ​ለው ዕወቅ።
6እርሱ የበ​ደ​ለ​ኞ​ችን ሕይ​ወት አያ​ድ​ንም፤
ለች​ግ​ረ​ኞች ግን ፍር​ዱን ይሰ​ጣል።
7ዐይ​ኑን ከጻ​ድ​ቃን ላይ አያ​ር​ቅም፤
ለዘ​ለ​ዓ​ለም ከነ​ገ​ሥ​ታት ጋር በዙ​ፋን ላይ ያስ​ቀ​ም​ጣ​ቸ​ዋል፥
በድል አድ​ራ​ጊ​ነ​ትም ያኖ​ራ​ቸ​ዋል።
እነ​ር​ሱም ከፍ ከፍ ይላሉ።
8በሰ​ን​ሰ​ለት እጃ​ቸ​ውን የታ​ሠሩ
በች​ግር ገመድ ይያ​ዛሉ።
9ሥራ​ቸ​ው​ንና መተ​ላ​ለ​ፋ​ቸ​ውን ይነ​ግ​ራ​ቸ​ዋል፥
ብዙ ነውና።
10ጻድ​ቃ​ንን ግን ይሰ​ማ​ቸ​ዋል፥
ከኀ​ጢ​አ​ትም ይመ​ለሱ ዘንድ ያዝ​ዛ​ቸ​ዋል።
11ቢሰ​ሙና ቢያ​ገ​ለ​ግ​ሉ​ትም፥
ዕድ​ሜ​አ​ቸ​ውን በመ​ል​ካም፥
ዘመ​ና​ቸ​ው​ንም በተ​ድላ ይፈ​ጽ​ማሉ።
12ኃጥ​ኣ​ንን ግን አያ​ድ​ና​ቸ​ውም
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያዩ ዘንድ አይ​ወ​ዱ​ምና፥
ሲገ​ሥ​ፃ​ቸ​ውም አይ​ሰ​ሙ​ምና።
13“ግብ​ዞች ግን በል​ባ​ቸው ቍጣን ያዘ​ጋ​ጃሉ፤
እር​ሱም ባሰ​ራ​ቸው ጊዜ አይ​ጮ​ኹም።
14ስለ​ዚ​ህም በሕ​ፃ​ን​ነ​ታ​ቸው ሳሉ ሰው​ነ​ታ​ቸው ትጠ​ፋ​ለች፥
ሕይ​ወ​ታ​ቸ​ው​ንም መላ​እ​ክት ያጠ​ፉ​አ​ታል።
15የተ​ቸ​ገ​ረ​ው​ንና ረዳት የሌ​ለ​ውን አስ​ጨ​ን​ቀ​ዋ​ልና፥
የየ​ዋ​ሃ​ን​ንም ፍርድ ለው​ጠ​ዋ​ልና።
16አን​ተን ግን ከጠ​ላ​ትህ አፍ አድ​ኖ​ሃል፥#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
በበ​ታ​ች​ህም ጥልቅ ባሕር፥ ፈሳሽ ምን​ጭም አለ፥
ማዕ​ድ​ህም በስብ ተሞ​ልታ ትወ​ር​ዳ​ለች።
17ፍር​ድን ለጻ​ድ​ቃን አያ​ዘ​ገ​ይ​ምና።
18ይበ​ድሉ ዘንድ በተ​ቀ​በ​ሉት መማ​ለጃ ኀጢ​አት ምክ​ን​ያት
ቍጣ በኃ​ጥ​ኣን ላይ ትመ​ጣ​ለች።#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
19በጭ​ን​ቀት ካሉ ከች​ግ​ረ​ኞች ልመና የተ​ነሣ
አእ​ም​ሮህ በፈ​ቃድ አያ​ስ​ትህ#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ይለ​ያል።
20በእ​ነ​ርሱ ፋንታ ወገ​ኖች እን​ዲ​ገቡ፥
ኀያ​ላን ሰዎ​ችን ሁሉ በሌ​ሊት አታ​ስ​ወጣ።
21መል​ካ​ምን አድ​ርግ እንጂ፥
ክፉን እን​ዳ​ት​ሠራ ተጠ​ን​ቀቅ።
ስለ​ዚ​ህም ከች​ግር ትድ​ና​ለህ።
22“እነሆ፥ ኀያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኀ​ይሉ ያጸ​ናል።
እንደ እር​ሱስ ያለ ኀያል ማን ነው?
23ሥራ​ው​ንስ የሚ​መ​ረ​ምር ማን ነው?
ወይስ፦ ክፉ ሠር​ተ​ሃል የሚ​ለው ማን ነው?
24ሰዎች ሊሠ​ሩት ከሞ​ከ​ሩት በላይ፥
ሥራው ታላቅ እንደ ሆነ አስብ።
25ሰው ሁሉ ራሱ፥
ኃጥ​ኣን ሙታን እንደ ሆኑ ያስ​ባል።
26እነሆ፥ ኀያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታላቅ ነው፥ እኛም አና​ው​ቀ​ውም፤
የዘ​መ​ኑም ቍጥር አይ​መ​ረ​መ​ርም።
27የዝ​ና​ቡም ነጠ​ብ​ጣ​ቦች በእ​ርሱ ይቈ​ጠ​ራሉ።
ዝና​ብም ከደ​መና ይን​ጠ​ባ​ጠ​ባል፤
28የጥ​ንቱ ይበ​ቅ​ላል።
ደመ​ናም በሟች ላይ ይጋ​ር​ዳል፥
ስፍር ቍጥር የሌ​ለው ዝናብ ይዘ​ን​ባል፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. የሚ​ከ​ተ​ለ​ውን ይጨ​ም​ራል “ ለእ​ን​ስ​ሳ​ትም ጊዜን ይወ​ስ​ናል ፤ እነ​ር​ሱም የዕ​ረ​ፍ​ትን ሥር​ዐት ያው​ቃሉ ፤ ይህ​ንም ሁሉ በማ​ወ​ቅህ አት​ደ​ነቅ ፤ አእ​ም​ሮ​ህም በሰ​ው​ነ​ትህ አይ​ታ​ወክ፤”
29አንድ ሰው የደ​መ​ና​ውን መዘ​ር​ጋት፥
ወይም የማ​ደ​ሪ​ያ​ውን ልክ ቢያ​ውቅ፥
30እነሆ፥ በዙ​ሪ​ያው ብር​ሃ​ኑን ይዘ​ረ​ጋል#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ቀስ​ቱን በእ​ርሱ ላይ ይዘ​ረ​ጋል” ይላል።
የባ​ሕ​ሩ​ንም ጥል​ቀት ይከ​ድ​ነ​ዋል።
31በእ​ነ​ዚህ በአ​ሕ​ዛብ ላይ ይፈ​ር​ዳል፤
ለኀ​ይ​ለ​ኛ​ውም ምግ​ቡን ይሰ​ጠ​ዋል።
32በእጁ ብር​ሃ​ንን ይሰ​ው​ራል፥#የግ​እዙ ምዕ. 36 ቍ. 32 እና 33 ግልጥ አይ​ደ​ለም።
አደጋ የሚ​ጥ​ል​ባ​ት​ንም አዘዘ።
33ስለ እር​ሱም ወዳጁ፥
በዐ​መ​ፃው ያገ​ኘ​ች​ውን ይና​ገ​ራል።

ማድመቅ

Share

Copy

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ