መጽ​ሐፈ ኢዮብ 18

18
የበ​ል​ዳ​ዶስ ንግ​ግር
1አው​ኬ​ና​ዊው#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሱሓ​ዊው” ይላል። በል​ዳ​ዶስ መለሰ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“ዝም የማ​ት​ለው እስከ መቼ ነው?
እኛም እን​ድ​ን​ነ​ግ​ርህ ታገሥ።
3ስለ ምንስ እንደ እን​ስሳ በፊ​ትህ ዝም አልን?
4መከ​ራው ይገ​ባ​ሃል፤ አን​ተስ የሞ​ትህ እንደ ሆነ ምን​ድን ነው?
ከሰ​ማይ በታች ምድር ስለ አንተ ባድማ ትሆ​ና​ለ​ችን?#ግእዙ “አል​ቦኑ ዘይ​ኄ​ይስ እም​ኔከ በታ​ሕተ ሰማይ” ይላል።
ወይስ ተራ​ራ​ዎች ከመ​ሠ​ረ​ታ​ቸው ይና​ወ​ጣ​ሉን?
5“የኀ​ጢ​ኣ​ተ​ኞች መብ​ራት ይጠ​ፋል፥
ነበ​ል​ባ​ላ​ቸ​ውም ብልጭ አይ​ልም።
6ብር​ሃኑ በድ​ን​ኳኑ ውስጥ ይጨ​ል​ማል፤
መብ​ራ​ቱም በላዩ ይጠ​ፋል።
7የተ​ዋ​ረዱ ሰዎች ንብ​ረ​ቱን ይወ​ስ​ዳሉ፤
ምክ​ሩም ትጥ​ለ​ዋ​ለች።
8እግሩ በወ​ጥ​መድ ትያ​ዛ​ለች፤
በመ​ረ​ብም ትታ​ሠ​ራ​ለች፤
9አሽ​ክ​ላ​ዎች በላዩ ይመ​ጣሉ፤
የተ​ጠ​ሙ​ትም በእ​ርሱ ይበ​ረ​ታሉ፤
10በም​ድር ላይ የሸ​ም​ቀቆ ገመዱ ተሰ​ው​ራ​ለች፤
የሚ​ጐ​ት​ተ​ውም በመ​ን​ገዱ ላይ ነው።
11መከራ በዙ​ሪ​ያው ታጠ​ፋ​ዋ​ለች፤
ብዙ ጠላ​ቶ​ችም ከእ​ግሩ በታች ይመ​ጣሉ።
12ኀይሉ በራብ ትደ​ክ​ማ​ለች።
አስ​ጨ​ናቂ መቅ​ሠ​ፍ​ትም ተዘ​ጋ​ጅ​ቶ​ለ​ታል።
13ጭኖቹ ይበ​ሰ​ብ​ሳሉ።
ሞትም መል​ካም ሕዋ​ሶ​ቹን ይበ​ላል።
14ጤን​ነት ከሥ​ጋው ትር​ቃ​ለች።
መከ​ራው ትጸ​ና​ለች፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ይበ​ቀ​ለ​ዋል።
15በሌ​ሊት በድ​ን​ኳኑ ውስጥ ለእ​ርሱ የማ​ይ​ሆ​ነው ይኖ​ራል፤
የእ​ር​ሱም መል​ካም ነገር በዲን ይበ​ተ​ናል።
16ሥሩ ከበ​ታቹ ይደ​ር​ቃል፤
ፍሬ​ውም ከላዩ ይረ​ግ​ፋል።
17መታ​ሰ​ቢ​ያ​ውም ከም​ድር ይጠ​ፋል፤
በም​ድ​ርም ስም አይ​ቀ​ር​ለ​ትም።
18ከብ​ር​ሃን ወደ ጨለማ አር​ቀው ያፈ​ል​ሱ​ታል።
19ከሕ​ዝቡ መካ​ከል የሚ​ራ​ራ​ለት የለም፤
ቤቱ ከሰ​ማይ በታች አይ​ቀ​ር​ለ​ትም።
20ነገር ግን ባዕድ በን​ብ​ረቱ ላይ ተድላ ያደ​ር​ጋል፤
ድሃው በእ​ርሱ ያጕ​ረ​መ​ር​ማል።
ፊተ​ኞ​ቹም ይደ​ነ​ቃሉ።
21የኀ​ጢ​ኣ​ተ​ኞች ቤት እን​ዲህ ነው፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም የማ​ያ​ውቁ ሰዎች ስፍራ ይህ ነው።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ