መጽ​ሐፈ ዕዝራ 6

6
የቂ​ሮስ ትእ​ዛዝ መገ​ኘት
1በዚያ ጊዜም ንጉሡ ዳር​ዮስ በባ​ቢ​ሎን ቤተ መዛ​ግ​ብት ያሉ የታ​ሪክ መጻ​ሕ​ፍት እን​ዲ​መ​ረ​መሩ አዘዘ። 2በሜ​ዶን አው​ራጃ ባለው ባሪ#ዕብ. “አሕ​መታ” ይላል። በሚ​ባል ከተማ በን​ጉሡ ቤት ውስጥ አንድ ጥቅ​ልል ተገኘ፤ በው​ስ​ጡም ይህ ነገር ለመ​ታ​ሰ​ቢያ ተጽፎ ነበር። 3በን​ጉሡ በቂ​ሮስ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት ንጉሡ ቂሮስ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ስላ​ለው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ እን​ዲህ ብሎ አዘዘ፥ “ይህ ቤት ይሠራ መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ቀ​ር​ብ​በ​ትም ቦታ ይሠራ፤#ዕብ. “በጽ​ኑም ይመ​ሥ​ረት” የሚል ይጨ​ም​ራል። ቁመ​ቱም ስድሳ ክንድ፥ ወር​ዱም ስድሳ ክንድ ይሁን። 4በሦ​ስት ተራ ታላ​ላቅ ድን​ጋይ፥ በአ​ንድ ተራ እን​ጨት ይደ​ረግ፤ ወጭ​ውም ከን​ጉሡ ቤት ይሰጥ። 5ናቡ​ከ​ደ​ነ​ዖ​ርም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ካለው መቅ​ደስ ወስዶ ወደ ባቢ​ሎን ያመ​ጣው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት የወ​ር​ቅና የብር ዕቃ ይሰጥ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ወዳ​ለው መቅ​ደስ ወደ ስፍ​ራው ይወ​ሰድ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ይኑር።
የቤተ መቅ​ደሱ ሥራ እን​ዲ​ቀ​ትል ንጉሥ ዳር​ዮስ ማዘዙ
6“አሁ​ንም አንተ በወ​ንዝ ማዶ ያለ​ኸው የሀ​ገሩ ገዥ ተን​ት​ናይ ደግሞ አሰ​ተ​ር​ቡ​ዝ​ናይ በወ​ንዝ ማዶም ያሉ ተባ​ባ​ሪ​ዎ​ቻ​ችሁ አፈ​ር​ስ​ካ​ው​ያን ከዚያ ራቁ፤#ምዕ. 6 ቍ. 6 በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. እና በግ​እዝ ልዩ​ነት አለው። 7ይህም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ይሠራ ዘንድ ተዉ፤ የአ​ይ​ሁ​ድም አለ​ቆ​ችና የአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ይህን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት በስ​ፍ​ራው ይሥሩ። 8ይህን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ዘንድ ለአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች የም​ታ​ደ​ር​ጉ​ትን፥ በወ​ንዝ ማዶ ካለው ሀገር ከሚ​መ​ጣው ግብር ከን​ጉሡ ገን​ዘብ ለእ​ነ​ዚህ ሰዎች ወጭ​ውን በት​ጋት እን​ድ​ት​ሰ​ጡ​አ​ቸው፥ ሥራም እን​ዳ​ታ​ስ​ፈ​ቱ​አ​ቸው አዝ​ዣ​ለሁ። 9ለሰ​ማይ አም​ላክ ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ያ​ስ​ፈ​ል​ገ​ውን ወይ​ፈ​ኖ​ችና አውራ በጎች፥ ጠቦ​ቶ​ችም፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም እን​ዳሉ እንደ ካህ​ናቱ ቃል ስን​ዴና ጨው፥ የወ​ይን ጠጅና ዘይት የሚ​ጠ​ይ​ቋ​ች​ሁን ዕለት ዕለት ስጡ​አ​ቸው። 10ይኸ​ውም ለሰ​ማይ አም​ላክ በጎ መዓዛ የሆ​ነ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ያቀ​ርቡ ዘንድ፥ ለን​ጉ​ሡና ለል​ጆ​ቹም ዕድሜ ይጸ​ልዩ ዘንድ ነው። 11ይህ​ንም ትእ​ዛዝ የሚ​ለ​ውጥ ሁሉ ምሰ​ሶው ከቤቱ ተነ​ቅሎ እርሱ ይሰ​ቀ​ል​በት፤ በላ​ዩም ይገ​ደል፤ ቤቱም የጕ​ድፍ መጣያ ይደ​ረግ ብዬ አዝ​ዣ​ለሁ። 12ስሙ በዚያ የሚ​ኖር አም​ላክ ይህን ይለ​ውጡ ዘንድ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ው​ንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ያፈ​ር​ሱት ዘንድ እጃ​ቸ​ውን የሚ​ዘ​ረ​ጉ​ትን ነገ​ሥ​ታ​ትና አሕ​ዛብ ሁሉ ያጥፋ። እኔ ዳር​ዮስ ይህን አዝ​ዣ​ለሁ፤ በት​ጋት ይፈ​ጸም።”
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ቅዳሴ
13ንጉ​ሡም ዳር​ዮስ እንደ ላከው ቃል፥ በዚ​ያን ጊዜ በወ​ንዝ ማዶ ያለ ገዥ ተን​ት​ናይ ደግሞ አስ​ተ​ር​ቡ​ዝ​ናይ ተባ​ባ​ሪ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም እን​ዲሁ ተግ​ተው አደ​ረጉ። 14የአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችና ሌዋ​ው​ያ​ንም በነ​ቢዩ በሐ​ጌና በአዶ ልጅ በዘ​ካ​ር​ያስ ትን​ቢት መሠ​ረት ሠሩ፤ ተከ​ና​ወ​ነ​ላ​ቸ​ውም። እንደ እስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ ትእ​ዛዝ፥ እንደ ፋር​ስም ነገ​ሥ​ታት እንደ ቂሮ​ስና እንደ ዳር​ዮስ፥ እንደ አር​ተ​ሰ​ስ​ታም#ዕብ. “አር​ጤ​ክ​ስስ” ይላል። ትእ​ዛዝ ሠር​ተው ፈጸሙ። 15ይህም ቤት በን​ጉሡ በዳ​ር​ዮስ መን​ግ​ሥት በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመት አዳር በሚ​ባል ወር በሦ​ስ​ተ​ኛው ቀን ተፈ​ጸመ።
16የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ፥ የቀ​ሩ​ትም የም​ር​ኮ​ኞች ልጆች የዚ​ህን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ቅዳሴ በደ​ስታ አደ​ረጉ። 17በዚ​ህም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ቅዳሴ መቶ ወይ​ፈ​ኖ​ችና ሁለት መቶ አውራ በጎች፥ አራት መቶም የበግ ጠቦ​ቶች አቀ​ረቡ፤ ስለ ኀጢ​አ​ትም መሥ​ዋ​ዕት እንደ እስ​ራ​ኤል ነገ​ዶች ቍጥር ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዐሥራ ሁለት አውራ ፍየ​ሎች አቀ​ረቡ። 18በሙ​ሴም መጽ​ሐፍ እንደ ተጻ​ፈው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ግ​ሎት ላይ ካህ​ና​ቱን በየ​ማ​ዕ​ር​ጋ​ቸው፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑ​ንም በየ​ክ​ፍ​ላ​ቸው አቆሙ።
19የም​ር​ኮ​ኞ​ቹም ልጆች በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በዐ​ሥራ አራ​ተ​ኛው ቀን ፋሲ​ካ​ውን አደ​ረጉ። 20ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያ​ኑም አንድ ሆነው ነጽ​ተው ነበር፤ ሁሉም ንጹ​ሓን ነበሩ፤ ለም​ር​ኮ​ኞ​ቹም ልጆች ሁሉ፥ ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ለካ​ህ​ናቱ፥ ለራ​ሳ​ቸ​ውም የፋ​ሲ​ካ​ውን በግ ዐረዱ። 21ከም​ር​ኮም ተመ​ል​ሰው የመ​ጡት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ይፈ​ልጉ ዘንድ ራሳ​ቸ​ውን ከም​ድር አሕ​ዛብ ርኵ​ሰት ለይ​ተው ወደ እነ​ርሱ መጥ​ተው የነ​በ​ሩት ሁሉ ፋሲ​ካ​ውን በሉ፤ 22እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ደስ አሰ​ኝ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ለመ​ሥ​ራት እጃ​ቸ​ውን ያጸና ዘንድ የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ልብ ወደ እነ​ርሱ መል​ሶ​አ​ልና የቂ​ጣ​ውን በዓል ሰባት ቀን በደ​ስታ አደ​ረጉ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ