መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 6

6
የቤተ መቅ​ደሱ ሥራ እን​ደ​ገና እንደ ተጀ​መረ
1በዳ​ር​ዮስ በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥቱ፦ ነቢ​ያቱ ሐጌና የሐዶ ልጅ ዘካ​ር​ያስ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባሉ አይ​ሁድ ላይ በእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም ትን​ቢት ተና​ገሩ። 2ከዚ​ህም በኋላ የሰ​ላ​ት​ያል ልጅ ዘሩ​ባ​ቤ​ልና የኤ​ዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ኢያሱ ተነሡ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ነቢ​ያት እየ​ረ​ዱ​አ​ቸው ከእ​ነ​ርሱ ጋር ሳሉ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ጀመሩ።
3በእ​ነ​ዚ​ያም ወራት የሶ​ር​ያና የፊ​ን​ቂስ ገዥ ሲሳ​ኒ​ስና ሳት​ራ​ቡ​ዛ​ኒስ ከባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ጋር ወደ እነ​ርሱ መጡ። 4እን​ዲ​ህም አሏ​ቸው፥ “ይህን ቤትና ጣራ​ውን፥ ሌላ​ው​ንም ሥራ ሁሉ ትሠሩ ዘንድ ማን አዘ​ዛ​ችሁ? የሚ​ሠ​ሩ​ትስ ግን​በ​ኞች እነ​ማን ናቸው?” 5ያን​ጊ​ዜም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይቅር ብሏ​ቸ​ዋ​ልና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምር​ኮ​ኞ​ቹን ጐብ​ኝ​ት​ዋ​ልና” ይላል። ለአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ሰጣ​ቸው። 6ወደ ዳር​ዮስ እስ​ኪ​ልኩ፥ ደብ​ዳ​ቤ​ንም እስ​ኪ​ያ​መ​ጡ​ላ​ቸው ድረስ ሥራ​ውን አል​ከ​ለ​ከ​ሏ​ቸ​ውም።
7የሶ​ር​ያና የፊ​ን​ቂስ ገዥ ሲሳ​ኒ​ስና ሳት​ራ​ቡ​ዛ​ኒስ፥ በሶ​ር​ያና በፊ​ን​ቂ​ስም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ያሉ ሹሞች፥ ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም “ለን​ጉሡ ለዳ​ር​ዮስ ትድ​ረስ” ብለው ወደ ዳር​ዮስ ጽፈው ላኩ። 8“ጌታ​ችን ንጉሥ ሆይ ሰላም ለአ​ንተ ይሁን! ሁሉን እን​ድ​ታ​ውቅ ወደ ይሁዳ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም በመ​ጣን ጊዜ የአ​ይ​ሁድ ምር​ኮ​ኞች አለ​ቆ​ችን በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ከተማ አገ​ኘ​ና​ቸው። 9በተ​ጠ​ረ​በና ዋጋው ብዙ በሆነ ድን​ጋይ፥ በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ማዕ​ዘን ባላ​ቸው እን​ጨ​ቶ​ችም ታላ​ቅና አዲስ የሆ​ነ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ሲሠሩ አገ​ኘ​ና​ቸው። 10በች​ኰ​ላም ይሠ​ሩና ያፋ​ጥኑ ነበር፤ በእ​ጃ​ቸ​ውም እያ​ስ​ተ​ካ​ከሉ በት​ጋት ይሠሩ ነበር። በክ​ብ​ርና በጥ​ን​ቃ​ቄም ተሠራ። 11ከዚ​ህም በኋላ ‘ይህን ቤት ትሠሩ ዘንድ፥ ይህ​ንም መሠ​ረት ትጥሉ ዘንድ ማን አዘ​ዛ​ችሁ?’ ብለን አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውን ጠየ​ቅ​ና​ቸው። 12ሰዎ​ቻ​ቸ​ው​ንና የሥራ መሪ​ዎ​ቻ​ቸ​ው​ንም በየ​ስ​ማ​ቸው ጽፈን ወደ አንተ እን​ልክ ዘንድ መረ​መ​ር​ና​ቸው፤ አለ​ቆ​ቻ​ች​ው​ንም ጠየ​ቅ​ና​ቸው። 13እነ​ር​ሱም እን​ዲህ ብለው መለ​ሱ​ልን፦ ‘እኛስ ምድ​ር​ንና ሰማ​ይን የፈ​ጠረ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሮች ነን።’ 14ይህ ቤት ከብዙ ዘመን አስ​ቀ​ድሞ በታ​ላ​ቁና በብ​ር​ቱው የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ሰሎ​ሞን ተሠ​ርቶ ተፈ​ጽሞ ነበር። 15ነገር ግን አባ​ቶ​ቻ​ችን ኀጢ​አት ሠር​ተው ሰማ​ያ​ዊ​ውን የእ​ስ​ራ​ኤል ፈጣሪ አሳ​ዝ​ነ​ው​ታ​ልና በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርና በፋ​ርስ ንጉሥ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በከ​ለ​ዳ​ው​ያን ንጉሥ” ይላል። እጅ ጣላ​ቸው። 16ይህ​ንም ቤት አፈ​ረሰ፤ በእ​ሳ​ትም አቃ​ጠለ፤ ሕዝ​ቡ​ንም ማረከ፤ ወደ ባቢ​ሎ​ንም ወሰ​ዳ​ቸው። 17ቂሮ​ስም በባ​ቢ​ሎን በነ​ገሠ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት ንጉሡ ቂሮስ ይህን ቤት ይሠሩ ዘንድ ጻፈ። 18ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ካለው ቤተ መቅ​ደስ ያወ​ጣ​ውን፥ ባዳ​ራ​ሹም ያኖ​ረ​ውን የወ​ር​ቅና የብር ንዋየ ቅድ​ሳ​ቱን፥ ንጉሥ ቂሮስ በባ​ቢ​ሎን ካለ አዳ​ራሹ አው​ጥቶ ለዘ​ሩ​ባ​ቤ​ልና ለገ​ዥው ለሰ​ና​ባ​ሶ​ርስ ሰጣ​ቸው። 19ይህ​ንም ንዋየ ቅድ​ሳት ወስ​ደው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለ ቤተ መቅ​ደስ ያኖ​ሩት ዘንድ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤተ መቅ​ደስ በቦ​ታው ይሠ​ሩት ዘንድ አዘ​ዛ​ቸው።#በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ምዕ. 6 ቍ. 19 በነ​ጠላ ነው። 20ከዚ​ህም በኋላ ያ ሰና​ባ​ሳ​ሮስ በደ​ረሰ ጊዜ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠራ ጀመረ፤ ከዚ​ያም ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ይሠሩ ነበር፤ ነገር ግን አል​ጨ​ረ​ሱም። 21አሁ​ንም ጌታ​ችን ንጉሥ ሆይ! በባ​ቢ​ሎን ያለ የን​ጉ​ሡን የቂ​ሮ​ስን መን​ግ​ሥት የታ​ሪክ መጻ​ሕ​ፍት ገል​ጠህ መር​ምር። 22ንጉሡ ቂሮስ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ዘንድ እንደ ፈቀደ ብታ​ገኝ፥ ጌታ​ችን ንጉሥ ሆይ! አን​ተም ፈቅ​ደ​ህ​ላ​ቸው እንደ ሆነ ስለ​ዚህ ነገር ላክ​ልን።”
የን​ጉሥ ቂሮስ ትእ​ዛዝ መገ​ኘት
23ከዚ​ህም በኋላ ንጉሡ ዳር​ዮስ በባ​ቢ​ሎን የታ​ሪክ መጽ​ሐፍ ውስጥ ይፈ​ልጉ ዘንድ አዘዘ፤ በሜ​ዶን አው​ራጃ በጣ​ኒስ-ባሪ ከተማ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ኤክ​ባ​ታና” ይላል። ውስጥ የታ​ሪክ መጽ​ሐ​ፉን ባኖ​ሩ​በት በአ​ንድ ቦታ ተገኘ፤ እን​ዲ​ህም ይላል፦ 24“በን​ጉሡ በቂ​ሮስ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመተ መን​ግ​ሥት በየ​ዕ​ለቱ በእ​ሳት መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሠ​ዉ​በ​ትን፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ዘንድ አዘዘ። 25ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወር​ዱም ስድሳ ክንድ ይሁን፤ ሥራ​ውም በሦ​ስት ወገን በጥ​ርብ ድን​ጋይ፥ ባን​ዲት ወገ​ንም በሀ​ገሩ አዲስ የዝ​ግባ እን​ጨት ይሁን፤ ወጭ​ው​ንም ከን​ጉሡ ከቂ​ሮስ ዕቃ ቤት ይሰ​ጧ​ቸው ዘንድ አዘዘ። 26ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ካለው ከቤተ መቅ​ደስ አው​ጥቶ ወደ ባቢ​ሎን የወ​ሰ​ደ​ውን የወ​ር​ቁ​ንና የብ​ሩን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ንዋየ ቅድ​ሳት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ወዳ​ለው ቀድሞ ወደ ነበ​ረ​በት ወደ​ዚያ ቤት ይመ​ል​ሱት ዘንድ አዘዘ።”
ንጉሥ ዳር​ዮስ ሥራው እን​ዲ​ቀ​ጥል ማዘዙ
27የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪያ የይ​ሁዳ አለቃ ዘሩ​ባ​ቤ​ልና በይ​ሁዳ ያሉ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት በቦ​ታው ይሠ​ሩት ዘንድ የሶ​ር​ያና የፊ​ን​ቂስ ገዥ ሲሳ​ኒ​ስና ሳት​ራ​ቡ​ዛ​ኒስ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋራ ያሉ ጓደ​ኞ​ቻ​ቸው የሶ​ር​ያና የፊ​ን​ቂስ ሹሞች ቦታ​ቸ​ውን ይተ​ዉ​ላ​ቸው ዘንድ አዘዘ፤ 28“እኔም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ሠር​ተው እስ​ኪ​ፈ​ጽሙ ድረስ ከተ​ማ​ረ​ኩ​በት የተ​መ​ለሱ የአ​ይ​ሁድ ወገ​ኖች ሁሉ አንድ ሁነው ተሰ​ማ​ር​ተው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ዘንድ አዘ​ዝ​ኋ​ቸው። 29ከቄሊ-ሶር​ያና ፊኒቂ ከሚ​ገ​ባው ግብር ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሥ​ዋ​ዕት ፍየ​ሎ​ች​ንና ላሞ​ችን፥ በጎ​ች​ንም እንደ ሥር​ዐቱ ለእ​ነ​ዚህ ሰዎ​ችና ለአ​ለ​ቃው ለዘ​ሩ​ባ​ቤ​ልም ሰጥ​ታ​ችሁ ደስ አሰ​ኙ​አ​ቸው። 30እን​ደ​ዚ​ሁም የሚ​ያ​ነ​ዱ​ትን እን​ጨት፥ ስን​ዴ​ውን፥ ጨዉ​ንና ወይ​ኑን፥ ዘይ​ቱ​ንም፥ የዘ​ወ​ት​ሩ​ንም ወጭ ገን​ዘብ ሁሉ፥ በየ​ዓ​መ​ቱም የሚ​ያ​ደ​ር​ሳ​ቸ​ውን፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያሉ ካህ​ናቱ ያሏ​ች​ሁን ያህል ስጧ​ቸው፤ ግብ​ሩ​ንም ሳት​ከ​ራ​ከሩ እነ​ርሱ የሚ​ሏ​ች​ሁን የሚ​በ​ቃ​ቸ​ውን ስጧ​ቸው። 31ስለ ንጉ​ሡና ስለ ልጆቹ ለል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍር​ባ​ኑን ያቀ​ርቡ ዘንድ፥ ስለ ሕይ​ወ​ታ​ቸ​ውም ይጸ​ል​ዩ​ላ​ቸው ዘንድ።
32“በዚች ደብ​ዳቤ እንደ ተጻፈ አል​ሠ​ራም የሚል፥ የሚ​ከ​ራ​ከ​ራ​ቸ​ውም ቢኖር ከራሱ ቤት እን​ጨት አም​ጥ​ተው በዚያ ይስ​ቀ​ሉት፤ ገን​ዘ​ቡ​ንም ይዝ​ረ​ፉት፤ ለን​ጉሡ ቤትም ይሁን። 33ስለ​ዚ​ህም ስሙ በዚያ የተ​ጠራ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ሥራ ይከ​ለ​ክ​ሏ​ቸው ዘንድ፥ ክፉ ሥራም ይሠሩ ዘንድ እጃ​ቸ​ውን የሚ​ያ​ነሡ ነገ​ሥ​ታ​ት​ንና አሕ​ዛ​ብን ሁሉ ያጥ​ፋ​ቸው። 34እኔ ዳር​ዮስ እን​ዲህ አድ​ር​ገው ተግ​ተው ይሠሩ ዘንድ አዘ​ዝሁ።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ