መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 5

5
ከም​ርኮ የተ​መ​ለ​ሱት ሰዎች ስም ዝር​ዝር
1ከዚ​ህም በኋላ የሚ​ወ​ጡ​ትን ያባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ቤተ ሰቦች አለ​ቆች በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው ለዩ፤ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን፥ ወን​ዶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንና ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ውን፥ ወን​ዶች አገ​ል​ጋ​ዮ​ቻ​ቸ​ው​ንና ሴቶች አገ​ል​ጋ​ዮ​ቻ​ቸ​ውን፥ ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለዩ። 2ዳር​ዮ​ስም በመ​ሰ​ንቆ፥ በበ​ገ​ናና በከ​በሮ በሰ​ላም ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ያደ​ር​ሷ​ቸው ዘንድ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ሺህ ፈረ​ሰ​ኞ​ችን ላከ። 3ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ሁሉ እየ​ዘ​ፈኑ ከእ​ነ​ርሱ ጋር በአ​ን​ድ​ነት እን​ዲ​ሄዱ አደ​ረገ።
4በየ​ሀ​ገ​ራ​ቸ​ውና በየ​ወ​ገ​ና​ቸው፥ አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውን ተከ​ት​ለው የወጡ ሰዎ​ችም ስማ​ቸው ይህ ነው። 5ካህ​ናት የፊ​ን​ሐስ ልጆች፥ የአ​ሮን ልጆች፥ የሰ​ራ​ህያ ልጅ የኢ​ዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ኢዮ​ስስ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ኢያሱ” ይላል። ከይ​ሁዳ ወገን ከፋ​ሬስ ወገን ከዳ​ዊት ወገን የሆነ የሰ​ላ​ት​ያል ልጅ የዘ​ሩ​ባ​ቤል ልጅ ኢዮ​አ​ቄም፤ 6ዘሩ​ባ​ቤ​ልም በፋ​ርስ ንጉሥ በዳ​ር​ዮስ ፊት በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥቱ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በሚ​ያ​ዝያ የጥ​በ​ብን ነገር የተ​ና​ገረ ነው።
7የባ​ቢ​ሎን ንጉሥ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ከማ​ረ​ካ​ቸው ከፋ​ርስ ምርኮ የወጡ ከይ​ሁዳ የሆኑ ሰዎች እኒህ ናቸው። 8እነ​ር​ሱም ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ወደ ሌላ​ዎች የይ​ሁዳ ክፍ​ሎች ተመ​ለሱ። ሁሉ​ንም በየ​ከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው ላካ​ቸው፤ እነ​ዚ​ህም አስ​ቀ​ድ​መው ከተ​ሾ​ሙ​ላ​ቸው ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዎቹ ሹሞች፥ ከኢ​ያ​ሱና ከዘ​ሩ​ባ​ቤል፥ ከነ​ህ​ምያ፥ ከዛ​ር​ያስ፥ ከሬ​ስ​ያስ፥ ከኤ​ኔ​ን​ዮስ፥ ከመ​ር​ዶ​ክ​ዮስ፥ ከቦ​ኤ​ል​ሰ​ሮስ፥ ከአ​ስ​ፈ​ራ​ሶስ፥ ከሬ​ል​ዮስ፥ ከኢ​ሮ​ም​ዮ​ስና ከበ​ዓ​ናስ ጋር የመጡ ናቸው። 9የሕ​ዝ​ቡም ቍጥር፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሕ​ዝ​ቡና የገ​ዢ​ዎች ቍጥር” ይላል። የፋ​ሬስ ልጆች ሁለት ሺ አንድ መቶ ሰባ ሁለት ናቸው፤ የሳ​ፋ​ንም ልጆች ሦስት መቶ ሰባ ሁለት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አራት መቶ ሰባ ሁለት” ይላል። ናቸው። 10የሐ​ሬስ ልጆ​ችም ሰባት መቶ አምሳ ስድ​ስት ናቸው። 11የፈ​ሓት ሞዓብ ልጆ​ችም ከሮ​ብ​አ​ምና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ኢዮ​አብ” ይላል። ከኢ​ዮ​ስስ ልጆች ጋራ ሁለት ሺ ስም​ንት መቶ ዐሥራ ሁለት ናቸው። 12የኤ​ላም ልጆች አንድ ሽህ ሁለት መቶ አምሳ አራት ናቸው፤ የዛ​ጦ​ንም ልጆች ዘጠኝ መቶ ስድሳ ናቸው፤ የኮ​ሮባ ልጆች ሰባት መቶ አምሳ ናቸው፤ የባ​ኒን ልጆ​ችም ስድ​ስት መቶ አርባ ስም​ንት ናቸው። 13የቤ​ባይ ልጆ​ችም ስድ​ስት መቶ ሠላሳ ሦስት ናቸው፤ የዓ​ዝ​ጋድ ልጆ​ችም ሺህ ሦስት መቶ ሃያ ሁለት ናቸው። 14የአ​ዶ​ኒ​ቃም ልጆች ስድ​ስት መቶ ስድሳ ሰባት ናቸው፤ የበ​ጉ​ዋይ ልጆ​ችም ሁለት ሺህ ስድሳ ሰባት ናቸው፤ የአ​ዲ​ኖ​ስም ልጆች አራት መቶ አምሳ አራት ናቸው። 15የአ​ዝ​ራ​ቅዮ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የአ​ጤር አዝ​ራ​ቅዩ ልጆች ዘጠና ሁለት” ይላል። የቄ​ላ​ንና የአ​ዛ​ጦን ልጆች ስድሳ ሰባት ናቸው፤ የአ​ዛሩ ልጆ​ችም አራት መቶ ሠላሳ ሁለት ናቸው። 16የሐ​ና​ን​ያም ልጆች መቶ አንድ ናቸው፤ የአ​ሮ​ምና የባ​ሕሴ ልጆች ሦስት መቶ ሃያ ሦስት ናቸው፤ 17የአ​ር​ስ​ፋ​ሪ​ስት ልጆች አንድ መቶ ዐሥራ ሁለት ናቸው። የበ​ጢ​ሩስ ልጆ​ችም ሦስት ሽህ አም​ስት ናቸው፤ የኤ​ና​ውም ልጆች መቶ አምሳ ስም​ንት#ግሪክ ሰባ. ሊ. የኤ​ና​ውን ልጆች አይ​ጽ​ፍም። ናቸው። የቤ​ት​ሎ​ሞን ልጆ​ችም መቶ ሃያ ሦስት ናቸው። 18ከኒ​ጤ​ባ​ስም ልጆች አምሳ አም​ስት፥ ከኤ​ና​ጦ​ስም ልጆች መቶ አምሳ ስም​ንት፥ የቤ​ት​ሳ​ሞስ ልጆች አርባ ሁለት፥ 19የቀ​ታ​ር​ቲ​ሐ​ር​ዮስ ልጆ​ችም ሃያ አም​ስት፥ የጳ​ሬ​ስና የፎ​ሮግ ልጆች ሰባት መቶ አርባ ሦስት ናቸው፤ 20አካ​ዲ​ያ​ስና አሚ​ዳ​ው​ያ​ንም አራት መቶ ሃያ ሁለት ናቸው፥ የቂ​ራ​ማና የጋ​ቢስ ልጆች ስድ​ስት መቶ ሃያ አንድ ናቸው። 21የመ​ቃ​ሉ​ንም ልጆች መቶ ሃያ ሁለት፥ ከቤ​ጠ​ሊም ልጆች አምሳ ሁለት፥ የኔ​ፋ​ስም መቶ አምሳ ስድ​ስት ናቸው። 22የቀ​ላ​ም​ሎ​ምና የሁ​ነስ ልጆች ሰባት መቶ ሃያ አም​ስት፥ የኤ​ሪካ ልጆች ሦስት መቶ አርባ አም​ስት፤ #ከግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የተ​ገኘ ነው። 23የሰ​ና​ሐ​ሰም ልጆች ሦስት ሺህ ሦስት መቶ አንድ ናቸው።
24የኢ​ዮ​ስስ ልጆች፥ ካህ​ና​ቱም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የኢ​ዮ​ስስ ልጅ የኤዱ ልጆች ካህ​ናት” ይላል። ከአ​ና​ሲብ ልጆች ጋራ ስም​ንት መቶ ሰባ ሁለት ናቸው። የኤ​ም​ሩት ልጆ​ችም ሁለት መቶ አምሳ ሁለት#“አንድ ሽህ አምሳ ሁለት” የሚ​ልም የግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ዘርዕ ይገ​ኛል። ናቸው። 25የፋ​ሰሩ ልጆ​ችም አንድ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት፥ የካ​ርሚ ልጆች#“የካ​ርሚ ልጆች” ከግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የተ​ገኘ ነው። ሽህ ዐሥራ ሰባት ናቸው።
26ሌዋ​ው​ያን ግን፦ የኢ​ዮ​ስስ የቆ​ድ​ሔሉ፥ የባ​ኑና የሱ​ዱይ ልጆች ሰባ አራት፤ 27መዝ​ሙር የሚ​ዘ​ምሩ የካ​ህ​ናት ልጆች፦ የአ​ሳፍ ልጆች መቶ ሃያ ስም​ንት፥ 28በረ​ኞች የሰ​ሎም ልጆች፦ የአ​ጤር ልጆች፥ የጤ​ል​ሞን ልጆች፥ የዓ​ቁብ ልጆች፥ የሐ​ጢጣ ልጆች፥ የሰ​ባይ ልጆች ሁሉም መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ናቸው።#“በረ​ኞች” አራት መቶ፥ “የዓ​ቁብ ልጆች” አንድ ሺህ ናቸው የሚል የግ​እዝ ዘርዕ ይገ​ኛል።
29የቤተ መቅ​ደስ አገ​ል​ጋ​ዮች፦ የኤ​ሳው ልጆች፥ የሓ​ሱፋ ልጆች፥ የጠ​ብ​ይት ልጆች፥ የቀ​ራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፥ የፋ​ዶን ልጆች፥ የሌ​ብና ልጆች፤ የአ​ባጋ ልጆች፥ 30የዐ​ቁድ ልጆች፥ የሐጡ ልጆች፥ የኪ​ጣብ ልጆች፥ የአ​ቀባ ልጆች፥ የሳ​ባዊ ልጆች፥ የሐና ልጆች፥ የቃ​ጡዓ ልጆች፥ የጌ​ዱር ልጆች፤ 31የያ​ሳሩ ልጆች፥ የዴ​ሳን ልጆች፥ የነ​ሒ​ሴቦ ልጆች፥ የካ​ሴባ ልጆች፥ የቀ​ዚራ ልጆች፥ የዖ​ዝያ ልጆች፥ የፋ​ኑሕ ልጆች፥ የአ​ዛራ ልጆች፥ የባ​ስቲ ልጆች፥ የአ​ስና ልጆች፥ የማ​አኒ ልጆች፥ የነ​ፋሲ ልጆች፥ የአ​ቁፋ ልጆች፥ የአ​ኪባ ልጆች፥ የአ​ሱር ልጆች፥ የፋ​ራ​ቂም ልጆች፥ የባ​ስ​ሊም ልጆች፤ 32የሚዳ ልጆች፥ የኩታ ልጆች፥ የሴ​ርያ ልጆች፥ የባ​ር​ኩስ ልጆች፥ የሴ​ሬር ልጆች፥ የቶ​ምሔ ልጆች፥ የናሲ ልጆች፥ የአ​ጢፍ ልጆች።
33የሰ​ሎ​ሞን አገ​ል​ጋ​ዮች ልጆች፦ የአ​ሳ​ፍ​ያት ልጆች፥ የፋ​ሬዳ ልጆች፥ የሐሊ ልጆች፥ የሎ​ዝን ልጆች፥ የያ​ሴ​ዳ​ሔል ልጆች፥ የሳ​ፋት ልጆች፤ 34የሐ​ጋያ ልጆች፥ የፈ​ቀ​ሬ​ተ​ሰ​ባይ ልጆች፥ የሳ​ሮ​ትዮ ልጆች፥ የማ​ሲ​ያስ ልጆች፥ የጋስ ልጆች፥ የአ​ዱስ ልጆች፥ የሱ​ባስ ልጆች፥ የአ​ፌራ ልጆች፥ የባ​ሩ​ዲስ ልጆች፥ የሳ​ፋጥ ልጆች፥ የአ​ሎም ልጆች፤
35እነ​ዚህ ቤተ መቅ​ደ​ሱን የሚ​ያ​ገ​ለ​ግሉ ሁሉና የሰ​ሎ​ሞን አገ​ል​ጋ​ዮች ልጆች ሁሉ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ናቸው።#“አራት ሺህ ሰባ ሁለት” የሚል የግ​እዝ ዘርዕ ይገ​ኛል።
36ከቴ​ል​ሜ​ሬ​ትና ከቴ​ሌ​ር​ሳስ የወ​ጡት ሁሉ፥ አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውም ካራ​ኃ​ታ​ንና ከሀ​ለር ናቸው። 37ሀገ​ራ​ቸ​ው​ንና ዘመ​ዳ​ቸ​ውን፥ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ወገን መሆ​ና​ቸ​ውን መና​ገር አል​ቻ​ሉም። የጡ​ባን ልጆች፥ የዱ​ዳን ልጆች፥ የነ​ቆ​ዲ​ንም ልጆች ስድ​ስት መቶ አምሳ ሁለት ናቸው።#“ዘጠኝ ሺህ አምሳ ሁለት” የሚል አን​ዳ​ንድ ዘርዕ ይገ​ኛል።
38ከካ​ህ​ናቱ ወገን የሆኑ፥ የክ​ህ​ነ​ትን ሥራ የሚ​ሠሩ፥ ተመ​ዝ​ግ​በው ያል​ተ​ገኙ፦ የሐ​ብያ ልጆች፥ የአ​ቅ​ቦስ ልጆች፥ ከቤ​ር​ዜሊ ልጆች ወገን በስሙ የተ​ጠ​ራች አው​ግ​ያን ያገባ የይ​ሆ​ድስ ልጆች ናቸው። 39የዘ​መ​ዶቹ ትው​ልድ ቍጥር በተ​ጻ​ፈ​በት መጽ​ሐፍ ትው​ል​ዱን ፈል​ገው አጡ፤ የክ​ህ​ነት አገ​ል​ግ​ሎ​ቱ​ንም አስ​ተ​ዉት። 40ነህ​ም​ያና ሐቴ​ር​ሳ​ታም፥ የክ​ህ​ነ​ትና የጽ​ድቅ ልብስ የሚ​ለ​ብስ ሊቀ ካህ​ናት እስ​ኪ​ሾሙ ድረስ ከተ​ቀ​ደ​ሰው ነገር ሁሉ እን​ዳ​ይ​ሰ​ጡት አዘ​ዙ​አ​ቸው።
41ከዐ​ሥራ ሁለት ዓመት በላይ ያሉት እስ​ራ​ኤል ሁሉ ከሴ​ቶች አገ​ል​ጋ​ዮ​ቻ​ቸ​ውና ከወ​ን​ዶች አገ​ል​ጋ​ዮ​ቻ​ቸው በቀር አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ። 42ወን​ዶ​ችና ሴቶች አገ​ል​ጋ​ዮ​ቻ​ቸ​ውም ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ነበሩ፤ ሴቶ​ችና ወን​ዶች መዘ​ም​ራ​ንም ሁለት መቶ አርባ አም​ስት ነበሩ። 43ግመ​ሎ​ቹም አራት መቶ ሠላሳ አም​ስት፥#“አራት መቶ አርባ ስድ​ስት ግመ​ሎች” የሚል ዘርዕ ይገ​ኛል። ፈረ​ሶ​ቹም ሰባት ሺህ ሠላሳ ስድ​ስት፥#“ሰባት ሺህ ሦስት መቶ አርባ ስድ​ስት” የሚል የግ​እዝ ዘርዕ ይገ​ኛል። በቅ​ሎ​ዎ​ችም ሁለት መቶ አርባ አም​ስት፥ አህ​ዮ​ችም አም​ስት ሺ አም​ስት መቶ ሃያ አም​ስት ነበሩ።
44ከሀ​ገ​ሮ​ቻ​ቸው አለ​ቆ​ችም ዐያ​ሌ​ዎች በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ወዳ​ለው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ በደ​ረሱ ጊዜ እን​ደ​ሚ​ቻ​ላ​ቸው መጠን ቤተ መቅ​ደ​ሱን በቦ​ታው ያቆ​ሙት ዘንድ ጸለዩ። 45ለቤተ መቅ​ደሱ የሥራ ጣጣም አንድ ሺህ ወቄት ወርቅ፥ አም​ስት ሺህ ወቄት ብርና መቶ የካ​ህ​ናት ልብስ ወደ ግምጃ ቤቱ ያገቡ ዘንድ ተሳሉ።
46ካህ​ና​ቱም፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና በአ​ካ​ባ​ቢዋ ከሚ​ኖሩ ሕዝ​ቦ​ችም፥ መዘ​ም​ራኑ፥ በር ጠባ​ቂ​ዎ​ቹም፥ እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ በየ​ቦ​ታ​ቸው ይቀ​መጡ ነበር።
ሥር​ዐተ አም​ል​ኮት እን​ደ​ገና መጀ​መሩ
47የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በያ​ገ​ራ​ቸው ተቀ​ም​ጠው ሳሉ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ በም​ሥ​ራቁ በር ዳርቻ ባለው አደ​ባ​ባይ በአ​ን​ድ​ነት ተሰ​በ​ሰቡ። 48የኢ​ዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ኢያ​ሱና ወን​ድ​ሞቹ ካህ​ናት፥ የሰ​ላ​ት​ያል ልጅ ዘሩ​ባ​ቤ​ልና ወን​ድ​ሞ​ቹም፥ ተነሡ፤ 49በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው በሙሴ መጽ​ሐፍ እንደ ተጻፈ እንደ ሕጉ መሥ​ዋ​ዕት ይሠዉ ዘንድ ለእ​ስ​ራ​ኤል ፈጣሪ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊ​ያ​ውን አዘ​ጋጁ። 50ሌሎ​ችም የም​ድር አሕ​ዛብ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ተሰ​ብ​ስ​በው በቦ​ታ​ቸው በመ​ሥ​ዊ​ያው አጠ​ገብ ተዘ​ጋጁ፤ ተሰ​ል​ፈው ነበ​ርና፤ ከዚ​ህም በኋላ የም​ድር አሕ​ዛ​ብን አሸ​ነ​ፏ​ቸው፤ በየ​ጊ​ዜው የሚ​ደ​ረ​ገ​ው​ንም የነ​ግ​ሁ​ንና የሠ​ር​ኩን መሥ​ዋ​ዕት ቍር​ባ​ኑ​ንም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቀ​ረቡ። 51በሕግ እንደ ተጻፈ የዳስ በዓ​ልን አደ​ረጉ፤ በየ​ዕ​ለ​ቱም እንደ ቀድ​ሞው መሥ​ዋ​ዕ​ቱን ሠዉ። 52ዳግ​መ​ኛም የዘ​ወ​ት​ሩን ቍር​ባ​ንና የሰ​ን​በ​ቱን መሥ​ዋ​ዕት፥ የመ​ባ​ቻ​ዎ​ች​ንና የተ​ቀ​ደ​ሱ​ትን በዓ​ላት መሥ​ዋ​ዕት አቀ​ረቡ። 53ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስእ​ለት የተ​ሳሉ ሰዎች ሁሉ ከሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ ጀምሮ መሥ​ዋ​ዕ​ቱን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያቀ​ርቡ ጀመሩ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤተ መቅ​ደስ ገና አል​ተ​ሠ​ራም ነበር። 54ደን​ጊያ ለሚ​ያ​ለ​ዝ​ቡና እን​ጨት ለሚ​ጠ​ርቡ ሰዎ​ችም ወር​ቅና ብር ሰጧ​ቸው፤ ለም​ግ​ባ​ቸ​ውም መብ​ሉ​ንና መጠ​ጡን ሰጧ​ቸው። 55የሲ​ዶ​ናና የጢ​ሮስ ሰዎ​ች​ንም የዋ​ን​ዛ​ውን እን​ጨ​ቶች ከሊ​ባ​ኖስ በኢ​ዮጴ ባሕር በኩል በመ​ር​ከብ ያገ​ቡ​ላ​ቸው ዘንድ አዘ​ዟ​ቸው፤ ከፋ​ርስ ንጉሥ ከቂ​ሮስ ዘን​ድም የት​እ​ዛዝ ደብ​ዳቤ ጻፉ​ላ​ቸው።
የቤተ መቅ​ደሱ መሠ​ረት እንደ ተጣለ
56ከዚህ በኋላ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በደ​ረሱ በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመት በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር የሰ​ላ​ት​ያል ልጅ ዘሩ​ባ​ቤል፥ የኢ​ዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ኢያሱ፥ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ካህ​ና​ቱና፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም፥ ከም​ርኮ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም የተ​መ​ለ​ሱ​ትም ሁሉ ቤተ መቅ​ደ​ስን ይሠሩ ዘንድ ጀመሩ። 57ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ወደ ይሁዳ በገቡ በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመት በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር መባቻ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደ​ስን መሠ​ረት አኖሩ። 58#“ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከሃያ ዓመት ጀምሮ ያሉ​ትን ሌዋ​ው​ያ​ንን ..” ይላል።ሌዋ​ው​ያ​ን​ንም በቤተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራ ላይ ሾሟ​ቸው፤ ኢያ​ሱና ልጆቹ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም፥ ወን​ድሙ አድ​ያ​ም​ያ​ልም፥ የኢ​ያሱ ልጅ ሄሜ​ዴ​ቦን፥ የኤ​ል​ያ​ዳን ልጅ የይ​ሁዳ ልጆች፥ ከል​ጆ​ቹና ከወ​ን​ድ​ሞቹ ጋር ሌዋ​ው​ያ​ንም ሁሉ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ይሠሩ ዘንድ የሥራ አለ​ቆች ሆነው በአ​ን​ድ​ነት ተሾሙ።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አና​ጢ​ዎ​ችም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ መቅ​ደስ ሠሩ” የሚል ይጨ​ም​ራል። 59ካህ​ና​ቱም ልብሰ ተክ​ህ​ኖ​ውን ለብ​ሰው፥ መሰ​ን​ቆ​ው​ንና መለ​ከ​ቱን ይዘው ቆሙ። የአ​ሳፍ ልጆች ሌዋ​ው​ያ​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በጸ​ና​ጽል ያመ​ሰ​ግኑ ነበር። 60በእ​ሴይ ልጅ በእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ በዳ​ዊት መዝ​ሙ​ርም ያመ​ሰ​ግ​ኑት ነበር። 61ጮኸ​ውም እያ​ስ​ተ​ዛ​ዘሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግኑ ነበር፤ ምስ​ጋ​ናው ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና፥ ቸር​ነ​ቱም በእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ላይ ነውና። 62የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ በመ​ነ​ሣቱ ሕዝቡ ሁሉ መለ​ከ​ቱን እየ​ነፉ፥ ከፍ ባለ ድም​ፅም እየ​ጮሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገኑ። 63ቀድሞ በዚያ በያ​ገ​ራ​ቸው ይኖሩ ከነ​በሩ ከካ​ህ​ና​ትና ከሌ​ዋ​ው​ያ​ንም የዚ​ያን ቤት ሥራ​ውን ቀድሞ ያዩት አለ​ቆ​ችም በታ​ላቅ ድምፅ ፈጽ​መው እያ​ለ​ቀሱ መጡ። 64ሕዝ​ቡም እስ​ኪ​ሰማ ድረስ ደስ ብሏ​ቸው ቀንደ መለ​ከት የሚ​ነፉ ብዙ ሰዎች ነበሩ። 65በሩቅ እስ​ኪ​ሰማ ድረስ በታ​ላቅ ድምፅ ቀንደ መለ​ከት የሚ​ነፉ ብዙ ሰዎች ነበ​ሩና ከሕ​ዝቡ ልቅሶ የተ​ነሣ የመ​ለ​ከ​ቱን ድምፅ አል​ሰ​ሙም። 66የይ​ሁ​ዳና የብ​ን​ያም ወገ​ኖች ጠላ​ቶ​ችም ያን በሰሙ ጊዜ የቀ​ንደ መለ​ከቱ ድምፅ ምን እንደ ሆነ ያውቁ ዘንድ መጡ። 67ከም​ርኮ የተ​መ​ለሱ እስ​ራ​ኤ​ልም የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ መቅ​ደስ እን​ደ​ሚ​ሠሩ ባወቁ ጊዜ፥ 68ወደ ዘሩ​ባ​ቤ​ልና ወደ ኢያሱ ወደ አገ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ሹሞች ሄደው እን​ዲህ አሏ​ቸው፥ “እኛ ከእ​ና​ንተ ጋራ እን​ሥራ፥ 69የአ​ሦር ንጉሥ ስል​ም​ና​ሶር#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አስ​ባ​ሳ​ሬት ንጉሠ አሦር” ይላል ግእዙ “ዐስበ ቀፈት ንጉሠ ፋርስ” ይላል። ወደ​ዚህ ካመ​ጣን ጀምሮ እንደ እና​ንተ ለፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችሁ እን​ገ​ዛ​ለ​ንና፥ መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንም ለእ​ርሱ እን​ሠ​ዋ​ለ​ንና።” 70ዘሩ​ባ​ቤ​ልና ኢያ​ሱም፥ የየ​ሀ​ገ​ሮ​ቻ​ቸው ሹሞ​ችም እን​ዲህ አሉ​አ​ቸው፥ “የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ጌታ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት መሥ​ራት ለእ​ኛም፥ ለእ​ና​ን​ተም አይ​ገ​ባ​ንም፤ 71ሐጌ እንደ ተና​ገረ፥ የፋ​ርስ ንጉሥ ቂሮ​ስም እን​ዳ​ዘ​ዘን የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ጌታ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ መቅ​ደስ እኛ ለብ​ቻ​ችን እን​ሠ​ራ​ለን።” 72የሚ​መ​ክቱ ያገሩ ሰዎች አሕ​ዛብ ግን በይ​ሁዳ ያሉ​ትን ፈጽ​መው ተሰ​ብ​ስ​በው ተዋ​ጓ​ቸው። 73አወ​ኳ​ቸው፤ ሥራ​ቸ​ው​ንም አስ​ቆሙ፤ በን​ጉሡ በቂ​ሮስ ዘመ​ንም ሁሉ እን​ዳ​ይ​ሠሩ ከለ​ከ​ሏ​ቸው፤ እስከ ዳር​ዮስ ሁለ​ተኛ ዓመተ መን​ግ​ሥ​ትም ድረስ ሥራ​ውን አስ​ተ​ዉ​አ​ቸው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ