መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 35

35
ንጉሡ ኢዮ​ስ​ያስ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የፋ​ሲ​ካን በዓል እንደ አከ​በረ
(2ነገ. 23፥21-23)
1ኢዮ​ስ​ያ​ስም ለአ​ም​ላኩ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ፋሲካ አደ​ረገ፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ወር በዐ​ሥራ አራ​ተ​ኛው ቀን የፋ​ሲ​ካ​ውን በግ አረዱ። 2ካህ​ና​ቱ​ንም በየ​ሥ​ር​ዐ​ታ​ቸው አቆመ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ አጸ​ና​ቸው። 3በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ መሥ​ራት የሚ​ች​ሉ​ትን ሌዋ​ው​ያን ራሳ​ቸ​ውን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲ​ያ​ነ​ጹና ቅድ​ስ​ቲ​ቱ​ንም ታቦት የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ የዳ​ዊት ልጅ ሰሎ​ሞን በሠ​ራው ቤት ውስጥ እን​ዲ​ያ​ኖሩ አዘ​ዛ​ቸው። ንጉ​ሡም ኢዮ​ስ​ያስ አለ፥ “በት​ከ​ሻ​ችሁ የም​ት​ሸ​ከ​ሙት አን​ዳች ነገር አይ​ኑር፤ አሁ​ንም አም​ላ​ካ​ች​ሁን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንና ሕዝ​ቡን እስ​ራ​ኤ​ልን አገ​ል​ግሉ፤ 4የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ ዳዊት እንደ አዘዘ፥ ልጁም ሰሎ​ሞን እንደ አዘዘ በየ​ሰ​ሞ​ና​ች​ሁና በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ ቤቶች ተዘ​ጋጁ፤ 5እንደ ሕዝ​ቡም ልጆች እንደ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ በየ​አ​ባ​ቶች ቤቶች አከ​ፋ​ፈል በመ​ቅ​ደሱ ቁሙ፤ እን​ዲ​ሁም ለሌ​ዋ​ው​ያን በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ቤት አከ​ፋ​ፈል ይሁን፤ 6የፋ​ሲ​ካ​ው​ንም በግ እረዱ፤ እና​ን​ተም ተቀ​ደሱ፥#“እና​ን​ተም ተቀ​ደሱ” የሚ​ለው በዕብ. ብቻ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሙሴ እጅ የተ​ና​ገ​ረ​ውን ቃል ታደ​ርጉ ዘንድ ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ አዘ​ጋጁ።”
7ኢዮ​ስ​ያ​ስም ለፋ​ሲ​ካው መሥ​ዋ​ዕት እን​ዲ​ሆን በዚያ ለነ​በ​ሩት ለሕ​ዝቡ ልጆች ከመ​ን​ጋው ሠላሳ ሺህ የበ​ግና የፍ​የል ጠቦ​ቶች፥ ሦስት ሺህም ወይ​ፈ​ኖች ሰጣ​ቸው፤ እነ​ዚ​ህም ከን​ጉሡ ሀብት ነበሩ። 8አለ​ቆ​ቹም ለሕ​ዝ​ቡና ለካ​ህ​ናቱ፥ ለሌ​ዋ​ው​ያ​ኑም በፈ​ቃ​ዳ​ቸው ሰጡ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አለ​ቆች፥ ኬል​ቅ​ያስ፥ ዘካ​ር​ያስ፥ ኢዮ​ሔል፥ ለፋ​ሲ​ካው መሥ​ዋ​ዕት እን​ዲ​ሆን ሁለት ሺህ ስድ​ስት መቶ በጎ​ች​ንና ፍየ​ሎ​ችን፥ ሦስት መቶም በሬ​ዎ​ችን ለካ​ህ​ናቱ ሰጡ። 9የሌ​ዋ​ው​ያ​ኑም አለ​ቆች ኮኒ​ን​ያስ በን​ያ​ስም፥#“በን​ያ​ስም” የሚ​ለው በግ​እ​ዝና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ብቻ። ወን​ድ​ሞ​ቹም ሰማ​ዕ​ያ​ስና ናት​ና​ኤል፥ ሰብ​ን​ያስ፥ ኢዮ​ሄል፥ ኢዮ​ዛ​ብድ ለፋ​ሲ​ካው መሥ​ዋ​ዕት እን​ዲ​ሆን አም​ስት ሺህ በጎ​ችን፥ አም​ስት መቶም በሬ​ዎ​ችን ለሌ​ዋ​ው​ያን ሰጡ።
10አገ​ል​ግ​ሎ​ቱም ተዘ​ጋጀ፤ ካህ​ና​ቱም በየ​ስ​ፍ​ራ​ቸው፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም በየ​ክ​ፍ​ላ​ቸው እንደ ንጉሡ ትእ​ዛዝ ቆሙ። 11የፋ​ሲ​ካ​ው​ንም በግ አረዱ፤ ካህ​ና​ቱም ከእ​ጃ​ቸው የተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ደም ረጩ፤ ሌዋ​ው​ያ​ኑም ቍር​በ​ቱን ገፈፉ። 12በሙ​ሴም መጽ​ሐፍ እንደ ተጻፈ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያቀ​ርቡ ዘንድ በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ቤቶች እንደ ክፍ​ላ​ቸው ለሕ​ዝቡ ልጆች እን​ዲ​ሰጡ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ለዩ። እን​ዲ​ሁም በበ​ሬ​ዎቹ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እን​ደ​ዚ​ሁም እስከ ጥዋት አደ​ረጉ” ይላል። አደ​ረጉ። 13የፋ​ሲ​ካ​ው​ንም በግ እንደ ሙሴ ሥር​ዐት በእ​ሳት ጠበሱ፤ የተ​ቀ​ደ​ሰ​ው​ንም ቍር​ባን በም​ን​ቸ​ትና በሰ​ታቴ፥ በድ​ስ​ትም ቀቀሉ፤ ተከ​ና​ወ​ነ​ላ​ቸ​ውም፤ ለሕ​ዝ​ቡም ልጆች ሁሉ በፍ​ጥ​ነት አደ​ረሱ። 14ከዚ​ያም በኋላ ለራ​ሳ​ቸ​ውና ከእ​ነ​ርሱ ጋር ላሉ ለካ​ህ​ናቱ አዘ​ጋጁ፤ የአ​ሮ​ንም ልጆች ካህ​ናቱ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና ስቡን ለማ​ቅ​ረብ እስከ ሌሊት ድረስ ይሠሩ ነበ​ርና ስለ​ዚህ ሌዋ​ው​ያን ለራ​ሳ​ቸ​ውና ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ለአ​ሮን ልጆች ለካ​ህ​ናቱ አዘ​ጋጁ። 15የአ​ሳ​ፍም ልጆች መዘ​ም​ራን እንደ ዳዊት፥ እንደ አሳ​ፍም፥ እንደ ኤማ​ንም የን​ጉ​ሡም ባለ ራእይ እንደ ነበ​ረው እንደ ኤዶ​ትም ትእ​ዛዝ በየ​ስ​ፍ​ራ​ቸው ነበሩ፤ በረ​ኞ​ቹም በሮ​ቹን ሁሉ ይጠ​ብቁ ነበር፤ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ሌዋ​ው​ያን ያዘ​ጋ​ጁ​ላ​ቸው ነበ​ርና ከአ​ገ​ል​ግ​ሎ​ታ​ቸው ይርቁ ዘንድ አያ​ስ​ፈ​ል​ጋ​ቸ​ውም ነበር።
16እንደ ንጉ​ሡም እንደ ኢዮ​ስ​ያስ ትእ​ዛዝ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ላይ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ያቀ​ርቡ ዘንድ፥ ፋሲ​ካ​ው​ንም ያደ​ርጉ ዘንድ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ግ​ሎት ሁሉ በዚያ ቀን ተዘ​ጋጀ። 17የተ​ገ​ኙ​ትም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች በዚያ ቀን ፋሲ​ካ​ውን፥ ሰባት ቀንም የቂ​ጣ​ውን በዓል አደ​ረጉ። 18ከነ​ቢ​ዩም ከሳ​ሙ​ኤል ዘመን ጀምሮ እን​ደ​ዚህ ያለ ፋሲካ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ከቶ አል​ተ​ደ​ረ​ገም፤ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ኢዮ​ስ​ያ​ስና ካህ​ናቱ፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም፥ በዚ​ያም የተ​ገኙ የይ​ሁ​ዳና የእ​ስ​ራ​ኤል ሰዎች ሁሉ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም የሚ​ኖ​ሩት እን​ዳ​ደ​ረ​ጉት ያለ ፋሲካ ያደ​ረገ የለም። 19ይህም ፋሲካ ኢዮ​ስ​ያስ በነ​ገሠ በዐ​ሥራ ስም​ን​ተ​ኛው ዓመት ተደ​ረገ።
19 ‘ሀ’ ንጉሡ ኢዮ​ስ​ያስ ካህኑ ኬል​ቅ​ያስ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ባገ​ኘው መጽ​ሐፍ የተ​ጻ​ፉ​ትን ቃላት ሁሉ ለመ​ጠ​በቅ አስ​ማ​ተ​ኞ​ች​ንና ጠን​ቋ​ዮ​ችን፥ ሟር​ተ​ኞ​ች​ንና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ምድ​ርና በይ​ሁዳ የሚ​ገ​ኙ​ትን ምስ​ሎ​ችና ቃሪ​ያ​ሲም የተ​ባሉ ጣዖ​ታ​ትን በእ​ሳት አቃ​ጠለ። 19 ‘ለ’ እንደ ሙሴ ሕግ ሁሉ በፍ​ጹም ልቡ፥ በፍ​ጹም ነፍሱ፥ በፍ​ጹም ኀይሉ ከእ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​መ​ለሰ የሚ​መ​ስ​ለው ሰው አል​ነ​በ​ረም። ከእ​ር​ሱም በኋላ የሚ​መ​ስ​ለው አል​ተ​ነ​ሣም። 19 ‘ሐ’ ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ንጉሥ ምናሴ በይ​ሁዳ ላይ በአ​ደ​ረ​ገ​ውና በአ​ነ​ሣ​ሣው ጥፋት ሁሉ ከአ​ስ​ከ​ተ​ለው ታላቅ ቍጣ አል​ተ​መ​ለ​ሰም። 19 ‘መ’ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለ፥ “እስ​ራ​ኤ​ልን እን​ዳ​ራ​ቅሁ ይሁ​ዳን ከፊቴ አር​ቃ​ለሁ። የመ​ረ​ጥ​ኋ​ት​ንም ከተማ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንና ስሜ በዚያ ይጠ​ራ​በ​ታል ያል​ሁ​ትን ቤት እጥ​ላ​ለሁ።”#ምዕ. 35 ከቍ. 19 “ሀ” እስከ 19 “መ” ያለው በዕብ. የለም። 20ከዚ​ህም ሁሉ በኋላ፥ ኢዮ​ስ​ያ​ስም ቤተ መቅ​ደ​ሱን ካሰ​ናዳ በኋላ፥#“ከዚህ ሁሉ በኋላ ኢዮ​ስ​ያ​ስም ቤተ መቅ​ደ​ሱን ካሰ​ናዳ በኋላ” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። የግ​ብጽ ንጉሥ ፈር​ዖን ኒካዑ በኤ​ፍ​ራ​ጥስ ወንዝ አጠ​ገብ#ዕብ. “ከር​ከ​ሚሽ ላይ” የሚል ይጨ​ም​ራል። የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ይዋጋ ዘንድ ወጣ፤ ኢዮ​ስ​ያ​ስም ሊጋ​ጠ​መው ወጣ። 21እር​ሱም፥ “የይ​ሁዳ ንጉሥ ሆይ፥ ከአ​ንተ ጋር ምን አለኝ? በም​ዋ​ጋ​በት በሌላ ቤት ላይ ነው እንጂ በአ​ንተ ላይ ዛሬ አል​መ​ጣ​ሁም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ድ​ቸ​ኩል አዝ​ዞ​ኛል፤ ከእኔ ጋር ያለው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ያ​ጠ​ፋህ ተጠ​ን​ቀቅ” ብሎ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላከ​በት። 22ኢዮ​ስ​ያስ ግን ይዋ​ጋው ዘንድ ተጽ​ናና እንጂ ፊቱን ከእ​ርሱ አል​መ​ለ​ሰም፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አፍ የተ​ነ​ገ​ረ​ውን የኒ​ካ​ዑን ቃል አል​ሰ​ማም፤ በመ​ጊ​ዶ​ንም ሸለቆ ይዋጋ ዘንድ መጣ። 23ቀስ​ተ​ኞ​ቹም ንጉ​ሡን ኢዮ​ስ​ያ​ስን ወጉት፤ ንጉ​ሡም ብላ​ቴ​ኖ​ቹን፥ “እጅግ ቈስ​ያ​ለ​ሁና ከሰ​ልፉ ውስጥ አው​ጡኝ” አላ​ቸው። 24ብላ​ቴ​ኖ​ቹም ከሰ​ረ​ገ​ላው አው​ር​ደው ለእ​ርሱ በነ​በ​ረው በሁ​ለ​ተ​ኛው ሰረ​ገላ ውስጥ አስ​ቀ​መ​ጡት፤ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም አመ​ጡት፤ እር​ሱም በዚያ ሞተ፤ በአ​ባ​ቶ​ቹም መቃ​ብር ተቀ​በረ፤ ይሁ​ዳና ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሁሉ ለኢ​ዮ​ስ​ያስ አለ​ቀሱ። 25ኤር​ም​ያ​ስም ለን​ጉሡ ለኢ​ዮ​ስ​ያስ የል​ቅሶ ግጥም ገጠ​መ​ለት፤ እስከ ዛሬም ድረስ ወን​ዶ​ችና ሴቶች መዘ​ም​ራን ሁሉ በል​ቅሶ ግጥ​ማ​ቸው ስለ ኢዮ​ስ​ያስ ይና​ገሩ ነበር፤ ይህም በእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዘንድ ወግ ሆኖ በል​ቅሶ ግጥም ተጽ​ፎ​አል። 26የቀ​ሩ​ትም የኢ​ዮ​ስ​ያስ ነገ​ሮች፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕግ እንደ ተጻፈ ያደ​ረ​ገው ቸር​ነት፥ 27የፊ​ተ​ኛ​ውና የኋ​ለ​ኛ​ውም ነገሩ፥ እነሆ፥ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልና በይ​ሁዳ ነገ​ሥ​ታት መጽ​ሐፍ ተጽ​ፈ​ዋል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ