መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 2:1-6

መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 2:1-6 አማ2000

ሰሎ​ሞ​ንም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም ቤት፥ ለራ​ሱም ቤተ መን​ግ​ሥት ልሥራ አለ። ሰሎ​ሞ​ንም የሚ​ሸ​ከ​ሙ​ትን ሰባ ሺህ፥ ከተ​ራ​ሮ​ችም ድን​ጋ​ዮ​ችን የሚ​ጠ​ር​ቡ​ትን ሰማ​ንያ ሺህ፥ በእ​ነ​ር​ሱም ላይ የተ​ሾ​ሙ​ትን ሦስት ሺህ ስድ​ስት መቶ ሰዎች ሰበ​ሰበ። ሰሎ​ሞ​ንም እን​ዲህ ሲል ወደ ጢሮስ ንጉሥ ወደ ኪራም ላከ፥ “ከአ​ባቴ ከዳ​ዊት ጋር እን​ዳ​ደ​ረ​ግህ፥ የሚ​ቀ​መ​ጥ​በ​ት​ንም ቤት ይሠራ ዘንድ የዝ​ግባ እን​ጨት እንደ ላክ​ህ​ለት፥ እን​ዲሁ ለእኔ አድ​ርግ። እነሆ፥ ለእ​ስ​ራ​ኤል ለዘ​ለ​ዓ​ለም እንደ ታዘ​ዘው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የጣ​ፋ​ጩን ሽቱ ዕጣን ለማ​ጠን፥ የገ​ጹ​ንም ኅብ​ስት ለማ​ኖር፥ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት በጥ​ዋ​ትና በማታ፥ በሰ​ን​በ​ታ​ቱም፥ በመ​ባ​ቻ​ዎ​ቹም፥ በአ​ም​ላ​ካ​ች​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓ​ላት ለማ​ቅ​ረብ እኔ ልጁ ለአ​ም​ላኬ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም ቤት እሠ​ራ​ለሁ፤ እር​ሱ​ንም እቀ​ድ​ሳ​ለሁ። አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከአ​ማ​ል​ክት ሁሉ ይልቅ ታላቅ ነውና የም​ሠ​ራው ቤት ታላቅ ነው። ነገር ግን ሰማ​ይና ከሰ​ማ​ያት በላይ ያለ ሰማይ ክብ​ሩን ይሸ​ከም ዘንድ አይ​ች​ል​ምና ለእ​ርሱ ቤት ይሠራ ዘንድ ማን ይች​ላል? በፊቱ ዕጣን ከማ​ጠን በቀር ቤት እሠ​ራ​ለት ዘንድ እኔ ማን ነኝ?