መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 2

2
የሰው አእ​ምሮ ውሱ​ን​ነት
1ስሙ ዑር​ኤል የተ​ባ​ለው ወደ እኔ የተ​ላ​ከው መል​አክ መለ​ሰ​ልኝ። 2“የል​ዑ​ልን#“በዚህ ዓለም የሚ​ሆ​ነ​ውን ነገር ልታ​ውቅ አት​ች​ልም” የሚል ዘርዕ ይገ​ኛል። የጌ​ት​ነ​ቱን ምክር ታገኝ ዘንድ ልቡ​ናህ ማድ​ነ​ቅን አደ​ነ​ቀን?” አለኝ። 3“አዎ ጌታዬ፥” አል​ሁት፤ እር​ሱም እን​ዲህ አለኝ፥ “ሦስ​ቱን መን​ገ​ዶች አሳ​ይህ ዘንድ፥ ሦስ​ቱ​ንም ምሳ​ሌ​ዎች በፊ​ትህ አኖር ዘንድ ተላ​ክሁ፥ 4ከእ​ነ​ዚ​ህም አን​ዲ​ቱን የተ​ረ​ጐ​ም​ህ​ልኝ እንደ ሆነ እኔም ታውቅ ዘንድ የም​ት​ወ​ዳ​ትን ይህ​ችን መን​ገድ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ ይህ ክፉ ልቡ​ናም ስለ​ምን እንደ ሆነ አስ​ተ​ም​ር​ሃ​ለሁ።”
5እኔም አል​ሁት፥ “አቤቱ ተና​ገር” እር​ሱም አለኝ፥ “እሳ​ቱን በሚ​ዛን መዝን፤ ነፋ​ሱ​ንም በመ​ስ​ፈ​ሪያ ስፈር፤ ያለ​ፈ​ች​ው​ንም ቀን ጥራት።”
6እኔም መልሼ እን​ዲህ አል​ሁት፥ “ስለ​ዚህ ነገር እኔን እንደ ጠየ​ቅ​ኸኝ ይህን ነገር ማድ​ረግ የሚ​ችል የተ​ፈ​ጠረ ሰው ማን ነው?” 7እር​ሱም አለኝ፥ “በባ​ሕር ውስጥ ምን ያህል ቤቶች አሉ? ወይም በጥ​ልቁ ውስጥ ምን ያህል ምን​ጮች አሉ? ወይም በሰ​ማ​ያት ላይ ምን ያህል መን​ገድ አለ? ወይም የሲ​ኦል መን​ገድ በየት ነው? ወይም የገ​ነት መን​ገድ በየት ነው? ብዬ ጠይ​ቄ​ህስ ቢሆን፥ 8ወደ ጥልቁ አል​ወ​ረ​ድ​ሁም፤ ወደ ሲኦ​ልም ፈጽሜ አል​ወ​ረ​ድ​ሁም፤ ወደ ሰማ​ይም አል​ወ​ጣ​ሁም ባል​ኸኝ ነበር። 9አሁን ግን ስለ ነፋ​ስና ስለ እሳት፥ ስላ​ለ​ፈ​ች​ውም ቀን እንጂ ይህን አል​ጠ​የ​ቅ​ሁ​ህም፤ እነሆ፥ ልታ​ው​ቀው አት​ች​ልም፤ ስለ እነ​ዚ​ህም የመ​ለ​ስ​ህ​ልኝ የለም። 10በአ​ንተ ዘንድ ያለ​ውን ማወቅ ያል​ቻ​ልህ፥ 11የል​ዑ​ልን የመ​ን​ገ​ዱን ሥር​ዐት እን​ዴት ማወቅ ትች​ላ​ለህ? የል​ዑል መን​ገዱ ፍጻሜ በሌ​ለው ተወ​ስ​ኗ​ልና፥ የም​ት​ፈ​ርስ፥ የም​ት​በ​ሰ​ብስ አንተ የማ​ይ​ፈ​ርስ፥ የማ​ይ​በ​ሰ​ብስ የል​ዑ​ልን መን​ገድ ማወቅ አት​ች​ልም።” 12ይህ​ንም በሰ​ማሁ ጊዜ በግ​ን​ባሬ ወደ​ቅሁ፤ “ተፈ​ጥ​ረን በኀ​ጢ​አት ከም​ን​ኖ​ርና መከ​ራን ከም​ን​ቀ​በል ባል​ተ​ፈ​ጠ​ርን በተ​ሻ​ለን ነበር፤ መከራ እን​ድ​ን​ቀ​በ​ልም አና​ው​ቅም” አል​ሁት።
የዛ​ፎ​ችና የባ​ሕር ምሳሌ
13መል​ሶም እን​ዲህ አለኝ፥ “ዛፍና የዱር እን​ጨ​ቶች ሄደው ምክ​ርን ተማ​ከሩ። 14ከፊ​ታ​ችን እና​ር​ቃት ዘንድ ኑ ሄደን ባሕ​ርን እን​ው​ጋት፤ ለዛ​ፍ​ነ​ታ​ች​ንም ሌላ ሀገር እና​ቅና” አሉ። 15እን​ደ​ዚ​ሁም የባ​ሕር ማዕ​በ​ላት ምክ​ርን መከሩ፤ “ለማ​ዕ​በ​ል​ነ​ታ​ችን በዚያ ሌላ ሀገር እን​ድ​ና​ቀና በም​ድረ በዳ ያለ ዛፍን እን​ወ​ጋው ዘንድ ኑ እን​ዝ​መት” አሉ። 16የዛ​ፎች ምክር ከንቱ ሆነ፤ እሳት ወጥታ በል​ታ​ቸ​ዋ​ለ​ችና። 17እን​ዲ​ሁም የባ​ሕር ማዕ​በ​ላት ምክር ከንቱ ሆነ፤ አሸ​ዋው ገድቦ ከል​ሎ​አ​ቸ​ዋ​ልና። 18“ፍርድ የም​ታ​ውቅ ከሆነ ከእ​ነ​ዚህ ማንን እው​ነ​ተኛ፥ ማን​ንስ ሐሰ​ተኛ ታደ​ር​ጋ​ለህ?” አለኝ።
19መል​ሼም እን​ዲህ አልሁ፥ “ሁለቱ ከን​ቱን ዐሰቡ፤ የብስ ለዛፍ፥ ባሕ​ርም ማዕ​በ​ልን ትሸ​ከም ዘንድ ተሰ​ጥ​ታ​ለ​ችና።”
20እር​ሱም መልሶ እን​ዲህ አለኝ፦“ መል​ካም ፈረ​ድህ፤ እን​ዲሁ ለራ​ስህ ለምን አት​ፈ​ር​ድም? 21የብስ ለዛፍ፥ ባሕ​ርም ለማ​ዕ​በ​ልዋ እንደ ተሰ​ጠች እን​ዲ​ሁም በም​ድር የሚ​ኖሩ ሰዎች በም​ድር ያለ​ውን ማወቅ ይች​ላሉ እንጂ በሰ​ማ​ያ​ትና ከሰ​ማ​ያት በላይ ያለ​ውን አይ​ደ​ለም።”
የዘ​መኑ ፍጻሜ
22መል​ሼም እን​ዲህ አል​ሁት፥ “አቤቱ እጠ​ይ​ቅ​ሃ​ለሁ፤ እን​ግ​ዲ​ያው እና​ስብ ዘንድ ልብ ለምን ተሰ​ጠን? 23እኔ ግን የል​ዑ​ልን መን​ገድ እጠ​ይቅ ዘንድ አል​ወ​ደ​ድ​ሁም፤ ሁል​ጊዜ በእኛ ላይ ስለ​ሚ​ያ​ል​ፈው እንጂ፤ እስ​ራ​ኤል በው​ር​ደት ለአ​ሕ​ዛብ፥ የወ​ደ​ድ​ኸ​ውም ሕዝብ ለኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ሕዝብ ተሰ​ጥ​ቶ​አ​ልና። የአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ንም ኦሪት ጠፍ​ታ​ለ​ችና፤ በው​ስ​ጧም የተ​ጻ​ፈው ቃል ኪዳን የለ​ምና። 24ከዓ​ለም እንደ አን​በጣ እና​ል​ፋ​ለን፤ ሕይ​ወ​ታ​ች​ንም እንደ ጢስ ነው፤ ምሕ​ረ​ት​ንም ለማ​ግ​ኘት የተ​ገ​ባን አይ​ደ​ለ​ንም። 25ነገር ግን በእኛ ስለ ተጠራ ስለ ቅዱስ ስሙ ምን እና​ደ​ር​ጋ​ለን? ስለ​ዚህ ነገር ጠየ​ቅ​ሁህ።”
26እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በሕ​ይ​ወት ካለህ ታየ​ዋ​ለህ፤ በሕ​ይ​ወት ብት​ኖ​ርም በጊ​ዜው ታው​ቀ​ዋ​ለህ፤ ዓለም ያልፍ ዘንድ ይቸ​ኩ​ላ​ልና። 27ዓለም የጻ​ድ​ቃ​ንን ተስፋ ማስ​ቀ​ረት አይ​ች​ል​ምና፥ ይህ ዓለም ጭን​ቅን የተ​ሞላ ነውና፥ ደዌ​ንም የተ​ሞላ ነውና። 28ስለ​እ​ርሷ የጠ​የ​ቅ​ኸኝ ክፋት ተዘ​ር​ታ​ለ​ችና፥ መከ​ር​ዋም አል​ደ​ረ​ሰ​ምና። 29በው​ስ​ጡም የተ​ዘ​ራው ካል​ታ​ጨ​ደና ካል​ተ​ነሣ ክፋት የተ​ዘ​ራ​ች​በት ቦታው አይ​ወ​ገ​ድም። 30በመ​ጀ​መ​ሪያ ክፉ የዘር ቅን​ጣት በአ​ዳም ልቡና ተዘ​ርቶ ነበ​ርና፥ የኀ​ጢ​አት ፍሬም ተወ​ል​ዷ​ልና እስከ ዛሬም ድረስ ደር​ሷ​ልና፥ መከ​ሩም እስ​ኪ​ደ​ርስ ድረስ ይወ​ለ​ዳል፤ 31አንተ ራስህ እስኪ አስ​በው! የክፉ ዘር ቅን​ጣት ቢዘራ ይህን ያህል የኀ​ጢ​አት ፍሬ ተወ​ለ​ደች። 32የመ​ል​ካም ዘር ቅን​ጣት ግን ብት​ዘራ ቍጥር የሌ​ለ​ውን መል​ካም ፍሬን እን​ዴት ባፈ​ራች ነበር!!”
33መል​ሼም እን​ዲህ አል​ሁት፥ “ደገ​ኛው እስከ መቼ ይሆ​ናል? የዚህ ዓለም ዘመኑ ክፉም፥ ጥቂ​ትም ነውና።” 34መል​ሶም እን​ዲህ አለኝ፥ “ከል​ዑል ይልቅ አንተ እጅግ የም​ት​ቸ​ኩል አይ​ደ​ለ​ህም፤ አን​ተስ ስለ ራስህ ትቸ​ኩ​ላ​ለህ፤ ልዑል ግን ስለ ብዙ​ዎች ይቸ​ኩ​ላል። 35ስለ​ዚህ የጻ​ድ​ቃን ነፍ​ሳት በማ​ደ​ሪ​ያ​ቸው ሁነው ጠየቁ፤ በዚህ እስከ መቼ ድረስ እን​ኖ​ራ​ለን? የዋ​ጋ​ች​ንስ መከር መቼ ይደ​ር​ሳል?” አሉ። 36መል​አኩ ኢይ​ሩ​ማ​ኤ​ልም#“ሊቀ መላ​እ​ክት ኢይ​ሩ​ማ​ኤ​ልም” የሚል ዘርዕ ይገ​ኛል። እን​ዲህ ብሎ መለ​ሰ​ላ​ቸው፥ “እንደ እና​ንተ ያሉት ጻድ​ቃን ቍጥ​ራ​ቸው በተ​ፈ​ጸመ ጊዜ ነው። 37ይህ ዓለም በሚ​ዛን ተመ​ዝ​ኗ​ልና፥ ባሕ​ሩ​ንም በመ​ስ​ፈ​ሪያ ሰፍ​ሮ​ታ​ልና፤ የተ​ሰ​ጠ​ውም መስ​ፈ​ርት እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ ዝም ይላል፤ አይ​ነ​ቃ​ምም።”
38እኔም መልሼ እን​ዲህ አል​ሁት፥ “አቤቱ ጌታዬ እነሆ፥ እኛ ሁላ​ችን ኀጢ​አ​ትን የተ​መ​ላን ነን፤ 39ምና​ል​ባት የጻ​ድ​ቃን የዋ​ጋ​ቸው መከር በእኛ ምክ​ን​ያት ይከ​ለ​ከ​ላ​ልን? ወይስ በዚህ ዓለም ስለ​ሚ​ኖ​ሩት ሰዎች ኀጢ​አት ነው?” 40እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ዘጠኝ ወር ከተ​ፈ​ጸመ በኋላ በማ​ኅ​ፀ​ንዋ ያለ​ውን ልጅ​ዋን ማስ​ቀ​ረት ይቻ​ላት እንደ ሆነ ሄደህ የፀ​ነ​ሰች ሴትን ጠይ​ቃት።” 41እኔም መልሼ አል​ሁት፥ “አቤቱ አት​ች​ልም፥” እር​ሱም አለኝ፥ “ሲኦ​ልና የጻ​ድ​ቃን ነፍ​ሳት ማደ​ሪ​ያ​ዎ​ችም እን​ዲሁ ናቸው። 42ማኅ​ፀን በምጥ ጊዜ ለመ​ው​ለድ እን​ደ​ም​ት​ቸ​ኩል ምድ​ርም ዓለም ከተ​ፈ​ጠረ ጀምሮ የተ​ቀ​በ​ሩ​ባት ሰዎ​ችን ትሰጥ ዘንድ ትቸ​ኩ​ላ​ለች። 43ያን​ጊ​ዜም ታውቅ ዘንድ የም​ት​ወ​ድ​ደ​ውን ነገር እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፥”
ምን ያህል ዘመን እንደ ቀረ
44እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “በፊ​ትህ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ካገ​ኘሁ፥ ልጠ​ይ​ቅም እን​ዲ​ቻ​ለኝ ካደ​ረ​ግ​ኸኝ ይኽን ንገ​ረኝ። 45ይመጣ ዘንድ ያለው ዘመን ባለ​ፈው ዘመን ልክ ነውን? ወይስ ያለ​ፈው ዘመን ይበ​ዛል? 46ያለ​ፈ​ውን አው​ቀ​ዋ​ለ​ሁና፥ የሚ​መ​ጣ​ውን ግን አላ​ው​ቀ​ው​ምና።” 47እር​ሱም አለኝ፥ “በቀኝ በኩል ባንድ ወገን ሁነህ ቁም፤ የም​ሳ​ሌ​ው​ንም ትር​ጓሜ አሳ​ይ​ሀ​ለሁ።” 48እኔም ቆምሁ፤ እነ​ሆም ምድጃ በፊቴ እየ​ነ​ደደ ሲሄድ አየሁ፤ ከዚ​ህም በኋላ እሳቱ በሄደ ጊዜ እነሆ ጢሱ ቀረ። 49ከእ​ር​ሱም በኋላ ውኃን የተ​መ​ላች ደመና በፊቴ ሄደች፤ ታላ​ቅና ብዙ የሆነ ዝና​ም​ንም ታዘ​ን​ማ​ለች፤ ታላቁ ዝና​ምም ካለፈ በኋላ ካፊ​ያው ቀረ። 50እር​ሱም አለኝ፥ “እን​ግ​ዲህ እስኪ አንተ ዐስ​በው፤ ከካ​ፊ​ያው ዝናሙ፥ ከጢሱ እሳቱ እን​ደ​ሚ​በዛ፥ እን​ደ​ዚ​ሁም ያለ​ፈው መስ​ፈ​ርት ይበ​ዛል፤ ነገር ግን ካፊ​ያ​ውም ጢሱም ይቀ​ራል።
51“እስከ እነ​ዚያ ዘመ​ኖች ድረስ እኖ​ራ​ለ​ሁን? እንጃ! በእ​ነ​ዚ​ያስ ወራ​ቶች ምን ይደ​ረ​ጋል?” ብዬ ማለ​ድ​ሁት። 52እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ስለ ጠየ​ቅ​ኸኝ ምል​ክ​ትስ ከብዙ በጥ​ቂቱ መን​ገር ይቻ​ለ​ኛል፤ ስለ ሕይ​ወ​ትህ ግን እነ​ግ​ርህ ዘንድ አል​ተ​ላ​ክ​ሁም፤ እኔም አላ​ው​ቀ​ውም።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ