መዝሙር 109:1-13

መዝሙር 109:1-13 NASV

የምስጋናዬ ምንጭ የሆንህ አምላክ ሆይ፤ ዝም አትበል፤ ክፉዎችና አታላዮች፣ አፋቸውን ከፍተውብኛልና፤ በውሸተኛ አንደበት ተናግረውብኛል። በጥላቻ ቃል ከብበውኛል፤ ያለ ምክንያትም ጥቃት አድርሰውብኛል። ስወድዳቸው ይወነጅሉኛል፤ እኔ ግን እጸልያለሁ። በበጎ ፈንታ ክፋትን፣ በወደድኋቸው ፈንታ ጥላቻን ይመልሱልኛል። ክፉ ሰው በላዩ ሹም፤ ከሳሽም በቀኙ ይቁም። ፍርድ ፊት ሲቆም በደለኛ ሆኖ ይገኝ፤ ጸሎቱም ለፍርድ ትሁንበት። ዕድሜው ይጠር፤ ሹመቱንም ሌላ ይውሰደው። ልጆቹ ድኻ አደጎች ይሁኑ፤ ሚስቱም መበለት ትሁን። ልጆቹ ይንከራተቱ፤ ለማኞችም ይሁኑ፤ ከፈረሰው ቤታቸውም ይሰደዱ። ያለውን ሁሉ ዕዳ ጠያቂ ይውረሰው፤ የድካሙንም ዋጋ ባዕዳን ይቀሙት። ማንም ሰው ምሕረት አያድርግለት፤ ለድኻ አደግ ልጆቹም የሚራራ አይኑር። ዘሩ ተለይቶ ይጥፋ፤ ስማቸውም በሚቀጥለው ትውልድ ይደምሰስ።