1
የዮሐንስ ወንጌል 15:5
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
እኔ የወይን ግንድ ነኝ፤ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና፤ በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።
Compare
የዮሐንስ ወንጌል 15:5 ખોજ કરો
2
የዮሐንስ ወንጌል 15:4
በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእንናተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንደማይችል፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ ማፍራት አትችሉም።
የዮሐንስ ወንጌል 15:4 ખોજ કરો
3
የዮሐንስ ወንጌል 15:7
በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ፤ ይሆንላችሁማል።
የዮሐንስ ወንጌል 15:7 ખોજ કરો
4
የዮሐንስ ወንጌል 15:16
እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንደሚሰጣችሁ፥ እንድትሄዱና ፍሬ እንድታፈሩ ፍሬአችሁም እንዲኖር ሾምኋችሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 15:16 ખોજ કરો
5
የዮሐንስ ወንጌል 15:13
ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።
የዮሐንስ ወንጌል 15:13 ખોજ કરો
6
የዮሐንስ ወንጌል 15:2
በእኔ ያለውን ፍሬ የማያፈራውን ቅርንጫፍ ሁሉ ያስወግደዋል፤ ፍሬ የሚያፈራውንም ሁሉ አብዝቶ እንዲያፈራ ያጠራዋል።
የዮሐንስ ወንጌል 15:2 ખોજ કરો
7
የዮሐንስ ወንጌል 15:12
“ትእዛዜ ይህች ናት፤ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ።
የዮሐንስ ወንጌል 15:12 ખોજ કરો
8
የዮሐንስ ወንጌል 15:8
ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ አባቴ ይከበራል።
የዮሐንስ ወንጌል 15:8 ખોજ કરો
9
የዮሐንስ ወንጌል 15:1
“እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው።
የዮሐንስ ወንጌል 15:1 ખોજ કરો
10
የዮሐንስ ወንጌል 15:6
በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል፤ ይደርቅማል፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል፤ ያቃጥሉአቸውማል።
የዮሐንስ ወንጌል 15:6 ખોજ કરો
11
የዮሐንስ ወንጌል 15:11
ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን፥ ደስታችሁም ፍጹም እንዲሆን ይህን ነግሬአችኋለሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 15:11 ખોજ કરો
12
የዮሐንስ ወንጌል 15:10
እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 15:10 ખોજ કરો
13
የዮሐንስ ወንጌል 15:17
እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ አዛችኋለሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 15:17 ખોજ કરો
14
የዮሐንስ ወንጌል 15:19
ከዓለም ብትሆኑ ኖሮ ዓለም የራሱ የሆነውን ይወድ ነበር፤ ነገር ግን እኔ ከዓለም መረጥኋችሁ እንጂ ከዓለም ስላልሆናችሁ ዓለም ይጠላችኋል።
የዮሐንስ ወንጌል 15:19 ખોજ કરો
હોમ
બાઇબલ
યોજનાઓ
વિડિઓઝ