YouVersion Logo
Search Icon

መዝ​ሙረ ዳዊት 140

140
የዳ​ዊት መዝ​ሙር።
1አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ፤ ስማኝ፤
ወደ አንተ ስጮ​ኽም የል​መ​ና​ዬን ቃል አድ​ምጥ።
2ጸሎ​ቴን በፊ​ትህ እንደ ዕጣን ተቀ​በ​ል​ልኝ፥
እጆቼ የሠ​ርክ መሥ​ዋ​ዕ​ትን አነሡ።#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “የእ​ጄ​ንም ማን​ሣት እንደ ሠርክ መሥ​ዋ​ዕት” ይላል።
3አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ፥
ለከ​ን​ፈ​ሮ​ቼም ጽኑዕ መዝ​ጊ​ያን አኑር።
4ልቤን ወደ ክፉ ነገር አት​መ​ል​ሰው፥
ዐመ​ፃን ከሚ​ያ​ደ​ርጉ ሰዎች ጋር
ለኀ​ጢ​አት ምክ​ን​ያት እን​ዳ​ል​ሰጥ፤
ከም​ር​ጦ​ቻ​ቸ​ውም ጋር አል​ተ​ባ​በር።
5በጽ​ድቅ ገሥ​ጸኝ፥ በም​ሕ​ረ​ትም ዝለ​ፈኝ፥
የኀ​ጢ​አ​ተኛ ዘይ​ትን ግን ራሴን አል​ቀ​ባም፤
ዳግ​መ​ኛም ጸሎቴ ይቅር እን​ዳ​ት​ላ​ቸው ነውና።#ዕብ. “ጸሎቴ ገና በክ​ፋ​ታ​ቸው ላይ ነው” ይላል።
6ኀያ​ላ​ኖ​ቻ​ቸው በዓ​ለት አጠ​ገብ ተጣሉ፥
ተች​ሎ​ኛ​ልና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ቃሌ ጣፋጭ ናትና” ይላል። ቃሌን ስሙኝ።
7እንደ ጓል በም​ድር ላይ ተሰ​ነ​ጣ​ጠቁ
እን​ዲሁ አጥ​ን​ቶ​ቻ​ቸው በሲ​ኦል ተበ​ተኑ፥
8አቤቱ፥ ጌታዬ፥ ዐይ​ኖቼ ወደ አንተ ናቸ​ውና፤
በአ​ንተ ታመ​ንሁ፥ ነፍ​ሴን አታ​ው​ጣት።
9ከሰ​ወ​ሩ​ብኝ ወጥ​መድ፥
ዐመ​ፃ​ንም ከሚ​ያ​ደ​ርጉ ሰዎች እን​ቅ​ፋት ጠብ​ቀኝ።
10እኔ ብቻ​ዬን እስ​ካ​ልፍ ድረስ
ኃጥ​ኣን በወ​ጥ​መ​ዳ​ቸው ይው​ደቁ።

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in