መዝሙር 57
57
መዝሙር 57
በጨካኝ ጠላቶች ዘንድ
57፥7-11 ተጓ ምብ – መዝ 108፥1-5
ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በዋሻ በነበረበት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ#57 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።።
1ማረኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረኝ፤
ነፍሴ አንተን መጠጊያ አድርጋለችና፤
በክንፎችህ ሥር እጠለላለሁ።
2ለእኔ ያሰበውን ወደሚፈጽምልኝ አምላክ፣
ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ።
3ከሰማይ ልኮ ያድነኛል፤
የረገጡኝን ያዋርዳቸዋል፤ ሴላ
እግዚአብሔር ምሕረቱንና ታማኝነቱን ይልካል።
4ነፍሴ በአንበሶች ተከብባለች፤
በሚዘነጣጥሉ አራዊት መካከል ወድቄአለሁ፤
እነዚህም፣ ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፣
ምላሳቸውም የተሳለ ሰይፍ የሆኑ ሰዎች ናቸው።
5እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤
ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።
6ለእግሬ ወጥመድን ዘረጉ፤
ነፍሴንም አጐበጧት፤
በመተላለፊያዬ ላይ ጕድጓድ ቈፈሩ፤
ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት። ሴላ
7እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤
ልቤ ጽኑ ነው፤
እቀኛለሁ፤ አዜማለሁ።
8ነፍሴ ሆይ፤ ንቂ!
በገናና መሰንቆም ተነሡ
እኔም በማለዳ እነሣለሁ።
9ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤
በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ፤
10ምሕረትህ እስከ ሰማያት ከፍ ብላለችና፤
ታማኝነትህም እስከ ደመናት ትደርሳለች።
11እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤
ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።
Currently Selected:
መዝሙር 57: NASV
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.