YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 150

150
መዝሙር 150
የምስጋና መዝሙር
1ሃሌ ሉያ።#150፥1 አንዳንዶች ከ6 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።
እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤
በታላቅ ጠፈሩ አወድሱት።
2ስለ ብርቱ ሥራው አመስግኑት፤
እጅግ ታላቅ ነውና ወድሱት።
3በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤
በበገናና በመሰንቆ ወድሱት።
4በከበሮና በሽብሸባ አመስግኑት፤
በባለ አውታር መሣሪያና በእንቢልታ አወድሱት።
5ተርገብጋቢ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት፤
ድምፀ መልካም በሆነ ጸናጽል ወድሱት።
6እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን።
ሃሌ ሉያ።

Currently Selected:

መዝሙር 150: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy