1
ምሳሌ 11:25
አዲሱ መደበኛ ትርጒም
ለጋስ ይበለጽጋል፤ ሌሎችን የሚያረካም ራሱ ይረካል።
Compare
Explore ምሳሌ 11:25
2
ምሳሌ 11:24
አንዱ በለጋስነት ይሰጣል፤ ሆኖም ይበልጥ ያገኛል፤ ሌላው ያለ መጠን ይሰስታል፤ ግን ይደኸያል።
Explore ምሳሌ 11:24
3
ምሳሌ 11:2
ትዕቢት ስትመጣ ውርደትም ትከተላለች፤ በትሑት ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች።
Explore ምሳሌ 11:2
4
ምሳሌ 11:14
በአመራር ጕድለት መንግሥት ይወድቃል፤ የመካሮች ብዛት ግን ድልን ርግጠኛ ያደርጋል።
Explore ምሳሌ 11:14
5
ምሳሌ 11:30
የጻድቅ ፍሬ የሕይወት ዛፍ ናት፤ ነፍሳትን የሚማርክም ጠቢብ ነው።
Explore ምሳሌ 11:30
6
ምሳሌ 11:13
ሐሜተኛ ምስጢር አይጠብቅም፤ ታማኝ ሰው ግን ምስጢር ይጠብቃል።
Explore ምሳሌ 11:13
7
ምሳሌ 11:17
ደግ ሰው ራሱን ይጠቅማል፤ ጨካኝ ግን በራሱ ላይ መከራ ያመጣል።
Explore ምሳሌ 11:17
8
ምሳሌ 11:28
በሀብቱ የሚታመን ሁሉ ይወድቃል፤ ጻድቃን ግን እንደ አረንጓዴ ቅጠል ይለመልማሉ።
Explore ምሳሌ 11:28
9
ምሳሌ 11:4
በቍጣ ቀን ሀብት ፋይዳ የለውም፤ ጽድቅ ግን ከሞት ትታደጋለች።
Explore ምሳሌ 11:4
10
ምሳሌ 11:3
ቅኖችን ትክክለኛነታቸው ትመራቸዋለች፤ ወስላቶች ግን በገዛ አታላይነታቸው ይጠፋሉ።
Explore ምሳሌ 11:3
11
ምሳሌ 11:22
በእርያ አፍንጫ ላይ እንደ ተሰካ የወርቅ ቀለበት፣ ማስተዋል የጐደላት ቈንጆ ሴት እንዲሁ ናት።
Explore ምሳሌ 11:22
12
ምሳሌ 11:1
እግዚአብሔር የተጭበረበረ ሚዛንን ይጸየፋል፤ ትክክለኛ መለኪያ ግን ደስ ያሰኘዋል።
Explore ምሳሌ 11:1
Home
Bible
Plans
Videos