ማሕልየ መሓልይ 3:1-5

ማሕልየ መሓልይ 3:1-5 የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) (አማ2000)

ሌሊት በም​ን​ጣፌ ላይ ነፍሴ የወ​ደ​ደ​ች​ውን ፈለ​ግ​ሁት፤ ፈለ​ግ​ሁት አላ​ገ​ኘ​ሁ​ትም። ጠራ​ሁት አል​መ​ለ​ሰ​ል​ኝም። እነ​ሣ​ለሁ በከ​ተ​ማ​ዪ​ቱም እዞ​ራ​ለሁ፥ ነፍሴ የወ​ደ​ደ​ች​ውን በገ​በ​ያና በአ​ደ​ባ​ባይ እፈ​ል​ጋ​ለሁ፤ ፈለ​ግ​ሁት አላ​ገ​ኘ​ሁ​ትም። ጠራ​ሁት አል​መ​ለ​ሰ​ል​ኝም። ከተ​ማ​ዪ​ቱን የሚ​ጠ​ብ​ቁት ጠባ​ቂ​ዎች አገ​ኙኝ፤ ነፍሴ የወ​ደ​ደ​ች​ውን አያ​ች​ሁ​ትን? አል​ኋ​ቸው። ከእ​ነ​ር​ሱም ጥቂት እልፍ ብዬ ያን​ጊዜ ነፍሴ የወ​ደ​ደ​ች​ውን አገ​ኘ​ሁት፥ ያዝ​ሁ​ትም፤ ወደ እና​ቴም ቤት፥ ወደ ወላጅ እና​ቴም እል​ፍኝ እስ​ካ​ገ​ባው ድረስ አል​ተ​ው​ሁ​ትም። እና​ንተ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ቈነ​ጃ​ጅት ሆይ፥ ወድዶ እስ​ኪ​ነሣ ፍቅ​ሬን እን​ዳ​ት​ቀ​ሰ​ቅ​ሱ​ትና እን​ዳ​ታ​ስ​ነ​ሡት፥ በም​ድረ በዳው ኀይ​ልና ጽን​ዐት አም​ላ​ች​ኋ​ለሁ።