መጽ​ሐፈ ሲራክ 8

8
1በእ​ጃ​ቸው እን​ዳ​ት​ወ​ድቅ
ከታ​ላ​ላ​ቆች ሰዎች ጋር አት​ከ​ራ​ከር።
2በብ​ል​ጽ​ግ​ናው ድል እን​ዳ​ያ​ደ​ር​ግህ ከባ​ለ​ጸጋ ጋር አት​ጣላ፥
ብዙ​ዎች ስለ ወርቅ ጠፍ​ተ​ዋ​ልና፤
የነ​ገ​ሥ​ታ​ትም ልቡና ድል ሆኖ​አ​ልና።
3ከተ​ና​ጋሪ ሰውም ጋር አት​ከ​ራ​ከር፤
ያለ​ዚያ በእ​ሳት ላይ እን​ጨት መከ​መ​ርህ ነው።
4እና​ትና አባ​ት​ህን እን​ዳ​ታ​ዋ​ርድ፥
ከአ​ላ​ዋቂ ሰው ጋር አት​ሣቅ።
5ከኀ​ጢ​አቱ የተ​መ​ለ​ሰ​ውን ሰው አት​ን​ቀ​ፈው፤
እኛ ሁላ​ች​ንም ኀጢ​አ​ተ​ኞች እን​ደ​ሆን ዐስብ።
6በር​ጅ​ናው ጊዜ ሰውን አታ​ቅ​ል​ለው፥
ከእኛ የማ​ያ​ረጅ የለ​ምና።
7በሞተ ሰው ደስ አይ​በ​ልህ፤
ሁላ​ች​ንም እን​ደ​ም​ን​ሞት ዐስብ።
8የብ​ል​ሆ​ችን ነገር አታ​ቃ​ልል፤
ጥበ​ብን በእ​ነ​ርሱ ዘንድ ታገ​ኛ​ለ​ህና፥ ምሳ​ሌ​ያ​ቸ​ውን ተማር።
መም​ህ​ራ​ን​ንም አገ​ል​ግል።
9የሽ​ማ​ግ​ሎ​ችን ምክ​ራ​ቸ​ውን ጠብቅ፤
እነ​ርሱ ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ተም​ረ​ዋ​ልና
አን​ተም ከእ​ነ​ርሱ ተማር፤
በኀ​ዘ​ን​ህም ጊዜ የም​ት​ና​ገ​ረ​ውን ታገ​ኛ​ለህ
የም​ት​መ​ል​ሰ​ው​ንም ታው​ቃ​ለህ።
10በእ​ሳ​ታ​ቸው እን​ዳ​ት​ቃ​ጠል፥
የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎ​ችን እሳት አት​ጫር።
11በአ​ን​ደ​በቱ ነገር እን​ዳ​ያ​ስ​ትህ፥
በተ​ሳ​ዳ​ቢና በጠ​ላት ዘንድ አት​ከ​ራ​ከር።
12ከአ​ንተ ለሚ​በ​ለ​ጽ​ገው አታ​በ​ድ​ረው፤
ብታ​በ​ድ​ረው ግን ገን​ዘ​ብ​ህን እን​ዳ​ጣህ ዕወቅ።
13ከአ​ንተ ለሚ​በ​ረ​ታ​ውም አቷ​ሰው፤
ብቷ​ሰው ግን አንተ ራስህ እን​ደ​ም​ት​ከ​ፍል ዐስብ።
14ከዳኛ ጋር አት​ከ​ራ​ከር፥
እንደ ክብሩ መጠን ፍር​ድን ይለ​ው​ጡ​ለ​ታ​ልና፤
15እን​ዳ​ይ​ደ​ፍ​ርህ ከደ​ፋር ሰው ጋራ መን​ገ​ድን አት​ሂድ፤
እርሱ ልቡ እንደ ወደደ ያደ​ር​ጋ​ልና
አን​ተም በእ​ርሱ ስን​ፍና ትሞ​ታ​ለህ።
16ከቍጡ ሰው ጋር አት​ከ​ራ​ከር፤
በእ​ርሱ ዘንድ ደም ማፍ​ሰስ እንደ ኢም​ንት ነውና፥
ረዳት ወደ​ሌ​ለ​በት ቦታም ይወ​ስ​ድ​ሃ​ልና
ከእ​ርሱ ጋር ወደ ምድረ በዳ አት​ውጣ።
17የሰ​ማ​ውን ነገር መጠ​በቅ አይ​ች​ል​ምና፥
ከአ​ላ​ዋቂ ሰው ጋራ አት​ማ​ከር።
18እን​ዴት እን​ደ​ሚ​ደ​ር​ስ​ብህ አታ​ው​ቅ​ምና፥
ጉዳ​ይ​ህን በባ​ዕድ ፊት አት​ና​ገር።
19ዋጋህ እን​ዳ​ይ​ጠ​ፋ​ብህ፥
ለሰው ሁሉ የል​ብ​ህን ምሥ​ጢር አት​ግ​ለጥ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ