መጽ​ሐፈ ሲራክ 7

7
1ክፋ​ትን አት​ሥ​ራት፤
ክፉም አያ​ገ​ኝ​ህም።
2ከበ​ደል ራቅ፥
እር​ሷም ራስዋ ካንተ ትር​ቃ​ለች።
3ሰባት እጥፍ አድ​ር​ገህ እን​ዳ​ት​ሰ​በ​ስ​ባት፥
በኀ​ጢ​አት ትልም አት​ዝራ።
4ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ግ​ሥ​ትን አት​ለ​ምን፤
ከን​ጉ​ሥም የክ​ብር ዙፋን አት​ለ​ምን።
5በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ጻድቅ ነኝ አት​በል፤
በን​ጉ​ሥም ዘንድ ብልህ ነኝ አት​በል።
6ዳኛ መሆ​ንን አት​ው​ደድ፤
እነሆ፥ በደ​ለ​ኛ​ውን ለመ​በ​ቀል አት​ች​ልም ይሆ​ናል፤
እነሆ፥ ለባ​ለ​ጸ​ጋም ታደላ ይሆ​ናል፤
በእ​ው​ነት ሥራ​ህም ላይ ኀጢ​አት ትሠ​ራ​ለህ።
7ያገ​ር​ህ​ንም ሰው አት​በ​ድል፤
ራስ​ህ​ንም በወ​ገ​ኖ​ችህ መካ​ከል አታ​ስት።
8በአ​ን​ዲ​ቱም ቢሆን ከቅ​ጣት አታ​መ​ል​ጥ​ምና፥
ሁለት ኀጢ​አት አንድ አድ​ር​ገህ አት​ሥራ።
9በመ​ባዬ ብዛት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀጢ​አ​ቴን ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​ል​ኛል፤
ለል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መባእ ከአ​ገ​ባሁ ይቅር ይለ​ኛል አት​በል።
10በም​ት​ጸ​ል​ይ​በት ጊዜ አት​ቸ​ኩል፥
ምጽ​ዋት መመ​ጽ​ወ​ት​ንም አታ​ቃ​ልል።
11የሚ​ያ​ሳ​ዝን፥ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝም አለና፥
ባዘነ ሰው አት​ሳቅ።
12በባ​ል​ን​ጀ​ራህ ሐሰ​ትን ተግ​ባር አታ​ድ​ርግ፤
በወ​ዳ​ጅ​ህና በባ​ል​ን​ጀ​ራ​ህም ላይ እን​ዲህ አታ​ድ​ርግ።
13በም​ንም ሁል​ጊዜ ሐሰ​ትን አት​ው​ደድ፥
ፍጻ​ሜዋ ይጎ​ዳ​ሃ​ልና።
14በሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎች መካ​ከል ብዙ ቃል አት​ና​ገር፤
በአ​ፍህ የተ​ና​ገ​ር​ኸ​ውን ስእ​ለ​ት​ህን አት​መ​ልስ፥ ቃል​ህ​ንም አት​ለ​ውጥ።
15የእ​ጅ​ህ​ንም ሥራ አታ​ቃ​ልል፥
ፈጣ​ሪ​ህም የሚ​ያ​በ​ቅ​ል​ል​ህን ቡቃ​ያ​ህን ቸል አት​በል።
16ብዙ ናቸው ብለህ
ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ጋር አንድ አት​ሁን።
17ጥፋት እን​ደ​ማ​ት​ዘ​ገይ ዐስብ፥
ሰው​ነ​ት​ህን ፈጽ​መህ አዋ​ር​ዳት፥
የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ፍዳ​ቸው ትልና እሳት ነውና።
18በእ​የ​ነ​ጋው ወዳጅ አት​ለ​ውጥ፤
ስለ ቀይ ወርቅ ወዳ​ጅ​ህን አትጣ።
19መወ​ደዷ ከወ​ርቅ ይወ​ደ​ዳ​ልና
ብል​ህና ደግ ሴትን አት​ጥላ።
20በእ​ው​ነት በሚ​ገ​ዛ​ልህ ቤተ ሰብህ ላይ፥
ስለ አንተ ሰው​ነ​ቱን አሳ​ልፎ በሚ​ሰጥ በም​ን​ደ​ኛ​ህም ላይ ክፉ ነገ​ርን አታ​ድ​ርግ።
21ብልህ ቤተ ሰብ​ህን እንደ ራስህ ውደ​ደው፤
ነጻ ታወ​ጣ​ውም ዘንድ ተስፋ ያደ​ረ​ገ​ህን ዋጋ​ውን አታ​ጥ​ፋ​በት።
22ሁል​ጊዜ ከብ​ት​ህን መፍ​ቀድ አት​ተው፤
ከእ​ነ​ርሱ የሚ​ጠ​ቅ​ም​ህን ወደ አንተ አቅ​ርብ።
23ልጆች ቢኖ​ሩህ ምከ​ራ​ቸው፤
ከሕ​ፃ​ን​ነ​ታ​ቸው ጀም​ረህ ትሕ​ት​ናን አስ​ተ​ም​ራ​ቸው።
24ሴቶች ልጆ​ችም ቢኖ​ሩህ ጠብ​ቃ​ቸው፤
አታ​ስ​ታ​ቸው፥ አት​ሣ​ቅ​ላ​ቸው፥ አታ​ባ​ብ​ላ​ቸ​ውም።
25ልጅ​ህን አቅመ ሔዋን ስታ​ደ​ርስ አጋ​ባት፥
ጠብ​ቃት፥ ታላቅ ሥራ​ንም ትፈ​ጽ​ማ​ለህ፥ ከድ​ካ​ምም ታር​ፋ​ለህ፥
ነገር ግን ለብ​ልህ ሰው አጋ​ባት።
26እንደ ራስህ የም​ት​ወ​ዳት ሚስት ብት​ኖ​ርህ አት​ፍ​ታት።
27በፍ​ጹም ልቡ​ናህ አባ​ት​ህን አክ​ብ​ረው፥
የእ​ና​ት​ህ​ንም ምጧን አት​ዘ​ንጋ።
28በእ​ነ​ር​ሱም ምክ​ን​ያት እንደ ተወ​ለ​ድህ ዐስብ፤
ስላ​ደ​ረ​ጉ​ል​ህስ ፋንታ ምን ታደ​ር​ግ​ላ​ቸ​ዋ​ለህ?
29በፍ​ጹም ሰው​ነ​ትህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍራው፤
ካህ​ና​ቱ​ንም አክ​ብ​ራ​ቸው።
30በፍ​ጹም ኀይ​ል​ህም ፈጣ​ሪ​ህን ውደ​ደው፤
የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሉ​ት​ንም አት​ተ​ዋ​ቸው።
31እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍራው፤
የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ለ​ውን ካህ​ኑ​ንም አክ​ብ​ረው፤
የታ​ዘ​ዘ​ልህ ዕድ​ሉ​ንም ስጠው፤
ቀዳ​ም​ያ​ቱ​ንና፥ ስለ ኀጢ​አት የሚ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕት፥
ወር​ቹ​ንም፥ ማታና ጧትም የሚ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕት፥
መጀ​መ​ሪያ የሚ​ወ​ለ​ደ​ው​ንም ከብት ስጠው።
32በረ​ከ​ትህ ፍጽ​ምት ትሆን ዘንድ
እጅ​ህን ለድሃ ዘርጋ።
33ስጦታ በሕ​ያው ሁሉ ፊት ጸጋ አለው፥
ስለ ሞተ ሰውም ምጽ​ዋት መስ​ጠ​ትን አት​ተው።
34ከሚ​ያ​ለ​ቅሱ ሰዎ​ችም አት​ለይ፥
ከሚ​ያ​ለ​ቅ​ሱም ጋር አል​ቅስ።
35ሕመ​ም​ተ​ኛ​ንም ሰው መጐ​ብ​ኘት ቸል አት​በል፥
በዚ​ህም ይወ​ዱ​ሃል።
36በተ​ና​ገ​ር​ኸው ነገር ሁሉ ፍጻ​ሜ​ህን ዐስ​ባት፥
ሁል​ጊ​ዜም አት​በ​ድል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ