መጽ​ሐፈ ሲራክ 3

3
ልጆች ለወ​ላ​ጆ​ቻ​ቸው ማድ​ረግ ያለ​ባ​ቸው ግዴታ
1ልጆች ሆይ፥ እኔን አባ​ታ​ች​ሁን ስሙኝ፥
በሕ​ይ​ወት ትኖሩ ዘንድ እን​ዲህ አድ​ርጉ፤
2እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አባ​ትን በል​ጆች ላይ አክ​ብ​ሯ​ልና።
የእ​ና​ት​ንም ሥል​ጣን በል​ጆ​ችዋ ላይ ከፍ ከፍ አድ​ር​ጎ​አ​ልና።
3አባ​ቱን የሚ​ያ​ከ​ብር ልጅ ኀጢ​አቱ ይሰ​ረ​ይ​ለ​ታል።
4እና​ቱ​ንም የሚ​ያ​ከ​ብ​ራት ልጅ ድልብ እን​ደ​ሚ​ያ​ደ​ልብ ነው።
5አባ​ቱን የሚ​ያ​ከ​ብር ልጅ በል​ጆቹ ደስ ይለ​ዋል፤
በሚ​ጸ​ል​ይ​በ​ትም ቀን ፈጣ​ሪው ይሰ​ማ​ዋል።
6አባ​ቱን የሚ​ያ​ከ​ብር ልጅ ዕድ​ሜው ይረ​ዝ​ም​ለ​ታል።
7እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ሰማ ልጅ እና​ቱን ያሳ​ር​ፋ​ታል።
8እንደ አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹም ለወ​ላጁ ይገ​ዛል።
9በረ​ከቱ ትደ​ር​ስህ ዘንድ
በቃ​ል​ህም በሥ​ራ​ህም አባ​ት​ህን አክ​ብ​ረው።
10የአ​ባት በረ​ከት የል​ጅን ቤት ያጸ​ና​ልና፥
የእ​ናት ርግ​ማን ግን መሠ​ረ​ትን ይነ​ቅ​ላል።
11አባ​ት​ህን በማ​ቃ​ለል አት​መካ፤
አባ​ት​ህን ማቃ​ለል ትም​ክ​ሕት አይ​ሆ​ን​ህ​ምና
ሰው በአ​ባቱ ክብር ይከ​ብ​ራል፤
የሰ​ውም ውር​ደቱ እና​ቱን በማ​ቃ​ለሉ ነው።
12ልጄ ሆይ፥ በእ​ር​ጅ​ናው ጊዜ አባ​ት​ህን ርዳው፥
በሕ​ይ​ወ​ቱም ሳለ አታ​ሳ​ዝ​ነው።
13ቢያ​ረጅ፥ አእ​ም​ሮ​ው​ንም ቢያጣ ለፈ​ቃዱ እሺ በለው፥
እን​ደ​ሚ​ቻ​ል​ህም አክ​ብ​ረው፥ በአ​ረ​ጀም ጊዜ አታ​ስ​ከ​ፋው፥
ዋጋ በመ​ቀ​በል ጊዜ አባ​ት​ህን መር​ዳ​ትህ አይ​ዘ​ነ​ጋ​ብ​ህ​ምና።
14ስለ ኀጢ​አ​ትም ፋንታ ጽድቅ ትሠ​ራ​ል​ሃ​ለች።
15በመ​ከ​ራ​ህም ቀን ይታ​ሰ​ብ​ል​ሃል፤
ፀሐይ በረ​ድን እን​ደ​ሚ​ያ​ቀ​ል​ጠው ኀጢ​አ​ቶ​ችህ እን​ደ​ዚሁ ይቀ​ል​ጣሉ።
16አባ​ቱን የሚ​ጥል ሰው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ደ​ሚ​ፀ​ርፍ ነው፤
እና​ቱን የሚ​ያ​ሳ​ዝ​ና​ትም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የተ​ረ​ገመ ነው።
ስለ ትሕ​ትና
17ልጄ ሆይ፥ ሥራህ በሃ​ይ​ማ​ኖ​ትህ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በየ​ዋ​ህ​ነት” ይላል። ይገ​ለጥ፤
እው​ነ​ተ​ኞች ሰዎ​ችም ይወ​ድ​ዱ​ሃል።
18እንደ ገና​ን​ነ​ትህ መጠን እን​ደ​ዚሁ ራስ​ህን አዋ​ርድ።
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ዋጋ​ህን ታገ​ኛ​ለህ።
19የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራው ታላቅ ነውና፥
በቅ​ዱ​ሳ​ንና#“ቅዱ​ሳን” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። በት​ሑ​ታን ዘንድ ይመ​ሰ​ገ​ናል።
20የሚ​በ​ረ​ታ​ብ​ህን አት​ፈ​ልግ፤
የማ​ት​ች​ለ​ው​ንም አት​መ​ር​ምር፤
21ነገር ግን የታ​ዘ​ዝ​ኸ​ውን ዐስብ።
በስ​ውር ያለው ግን አያ​ስ​ጨ​ን​ቅህ።
22አላ​ስ​ፈ​ላጊ ሥራ​ዎ​ችን አት​መ​ራ​መር፤
ከሰ​ዎች ይልቅ ለአ​ንተ እጅግ ተገ​ል​ጦ​ል​ሃ​ልና።
23ብዙ ሰዎ​ችን መታ​በ​ያ​ቸው አሳ​ታ​ቸው።
ብዙ ሰዎ​ች​ንም የል​ቡ​ና​ቸው ትዕ​ቢት ጣላ​ቸው።
24ጥፋ​ትን የሚ​ወ​ዳት በእ​ርሷ ይሞ​ታል፥
ክፉ ልቡ​ናም በመ​ጨ​ረ​ሻው ይታ​መ​ማል።
25ክፉ ልቡና በመ​ከራ ይገ​ረ​ፋል፤
ኀጢ​አ​ተኛ ሰውም በኀ​ጢ​አቱ ላይ ኀጢ​አ​ትን ይጨ​ም​ራል።
26ለት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ጥፋት ፈውስ የላ​ትም፤
ክፉ ተክል በው​ስ​ጣ​ቸው ሥር ሰድ​ዶ​አ​ልና።
27የብ​ልህ ሰው ልቡና ምሳ​ሌን ይተ​ረ​ጕ​ማል፤
የዐ​ዋቂ ሰው ጆሮም ጥበብ መስ​ማ​ትን ትወ​ዳ​ለች።
ስለ ምጽ​ዋት
28የም​ት​ነ​ድድ እሳ​ትን ውኃ ያጠ​ፋ​ታል።
ምጽ​ዋ​ትም ኀጢ​አ​ትን ታስ​ተ​ሰ​ር​ያ​ለች።
29ምጽ​ዋ​ትን ለሚ​ሰጥ ሰው በመ​ጨ​ረሻ ይታ​ሰ​ብ​ለ​ታል፤
በሚ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ል​በ​ትም ጊዜ መጠ​ጊ​ያን ያገ​ኛል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ