ኦሪት ዘሌ​ዋ​ው​ያን 11

11
ስለ​ሚ​በ​ሉና ስለ​ማ​ይ​በሉ እን​ስ​ሳት
(ዘዳ. 14፥3-21)
1እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴ​ንና አሮ​ንን እን​ዲህ ብሎ ተና​ገ​ራ​ቸው፦ 2“ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ዲህ ብላ​ችሁ ንገ​ሩ​አ​ቸው፦ በም​ድር ካሉት እን​ስ​ሳት ሁሉ የም​ት​በ​ሉ​አ​ቸው እን​ስ​ሳት እነ​ዚህ ናቸው። 3የተ​ሰ​ነ​ጠቀ ሰኰና ያለ​ው​ንና የሚ​ያ​መ​ሰ​ኳ​ውን እን​ስሳ ሁሉ ብሉ። 4ነገር ግን ከሚ​ያ​መ​ሰ​ኩት ፥ ሰኰ​ና​ቸ​ውም ስን​ጥቅ ከሆ​ነው ከእ​ነ​ዚህ አት​በ​ሉም፤ ግመል ያመ​ሰ​ኳል፤ ነገር ግን ሰኰ​ናው ስላ​ል​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው። 5ጥን​ቸል ያመ​ሰ​ኳል፤ ነገር ግን ሰኰ​ናው ስላ​ል​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ ይህ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው። 6ሽኮኮ ያመ​ሰ​ኳል፤ ነገር ግን ሰኰ​ናው ስላ​ል​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው። 7እር​ያም ሰኰ​ናው ተሰ​ን​ጥ​ቆ​አል፤ ነገር ግን ስለ​ማ​ያ​መ​ሰኳ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው። 8የእ​ነ​ዚ​ህን ሥጋ አት​በ​ሉም፤ በድ​ና​ቸ​ው​ንም አት​ነ​ኩም፤ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው።
9“በውኃ ውስጥ ከሚ​ኖ​ሩት ሁሉ እነ​ዚ​ህን ትበ​ላ​ላ​ችሁ፤ በው​ኆች፥ በባ​ሕ​ሮ​ችም፥ በወ​ን​ዞ​ችም ውስጥ ከሚ​ኖ​ሩት ሁሉ ክን​ፍና ቅር​ፊት ያላ​ቸ​ውን ትበ​ላ​ላ​ችሁ። 10በው​ኆች ውስጥ ከሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀሱ፥ በው​ኆች ውስጥ የሕ​ይ​ወት ነፍስ ከአ​ላ​ቸው ሁሉ፥ በባ​ሕ​ሮ​ችና በወ​ን​ዞች ውስጥ ክን​ፍና ቅር​ፊት የሌ​ላ​ቸው ሁሉ በእ​ና​ንተ ዘንድ የተ​ጸ​የፉ ናቸው። 11በእ​ና​ን​ተም ዘንድ የተ​ጸ​የፉ ይሆ​ናሉ። ሥጋ​ቸ​ው​ንም አት​በ​ሉም፤ በድ​ና​ቸ​ው​ንም ትጸ​የ​ፋ​ላ​ችሁ። 12ክን​ፍና ቅር​ፊ​ትም የሌ​ላ​ቸው በውኃ ውስጥ የሚ​ኖ​ሩት ሁሉ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው።
13“ከወ​ፎ​ችም ወገን የም​ት​ጸ​የ​ፉ​አ​ቸው እነ​ዚህ ናቸው፤ አይ​በ​ሉም፤ የተ​ጸ​የፉ ናቸው፤ ንስር፥ ገዴ አሞራ፥ ዓሣ አውጭ፥ 14ጭላት፥ ጭል​ፊት፥ አንጭ አሞራ በየ​ወ​ገኑ፤ 15ቁራ ሁሉ በየ​ወ​ገኑ፤ 16ሰጎን በየ​ወ​ገኑ፤ ጠለቋ፥ ዝዪ፥ በቋል በየ​ወ​ገኑ፤ 17ጉጉት፥ እር​ኩም፥ ጋጋኖ፥ 18የውኃ ዶሮ፥ ይብራ፥ ጥምብ አንሣ አሞራ፥ 19ሸመላ፥ ሳቢሳ በየ​ወ​ገኑ፤ ጅን​ጅ​ላቴ ወፍ፥ የሌ​ሊት ወፍ።
20“የሚ​በ​ር​ርም፥ በአ​ራት እግ​ሮ​ችም የሚ​ሄድ ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ ሁሉ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው። 21ነገር ግን ከሚ​በ​ር​ሩት፥ አራ​ትም እግ​ሮች ካሉ​አ​ቸው፥ ከእ​ግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም በላይ በም​ድር ላይ የሚ​ዘ​ል​ሉ​ባ​ቸው ጭኖች ካሉ​አ​ቸው ተን​ቀ​ሳ​ቃ​ሾች እነ​ዚ​ህን ትበ​ላ​ላ​ችሁ፤ 22ከእ​ነ​ር​ሱም እነ​ዚ​ህን አት​በ​ሉም፤ ኩብ​ኩባ የሚ​መ​ስ​ለ​ውም፥ ፌንጣ የሚ​መ​ስ​ለ​ውም፥ አሸን የሚ​መ​ስ​ለ​ውም፥ አን​በጣ የሚ​መ​ስ​ለ​ውም።#ምዕ. 11 በቍ. 22 የተ​ገ​ለ​ጹት በዕብ. እና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. “የሚ​በሉ ናቸው” 23የሚ​በ​ርር፥ አራ​ትም እግ​ሮች ያሉት ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ ሁሉ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው።
24“በእ​ነ​ዚ​ህም ርኩስ ትሆ​ና​ላ​ችሁ፤ የእ​ነ​ር​ሱ​ንም በድን የሚ​ነካ ሁሉ እስከ ማታ ርኩስ ነው። 25ከእ​ነ​ር​ሱም በድን የሚ​ያ​ነሣ ሁሉ ልብ​ሱን ይጠብ፤ እስከ ማታም ርኩስ ነው። 26ሰኰ​ናም ያለው፥ ነገር ግን ሰኰ​ናው ያል​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ፥ የማ​ያ​መ​ሰ​ኳም እን​ስሳ ሁሉ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው፤ እር​ሱን የሚ​ነካ ሁሉ ርኩስ ነው። 27በአ​ራት እግ​ሮቹ ከሚ​ሄድ እን​ስሳ ሁሉ በመ​ዳ​ፎቹ ላይ የሚ​ሄድ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው፤ የእ​ር​ሱን በድን የሚ​ነካ ሁሉ እስከ ማታ ርኩስ ነው። 28በድ​ና​ቸ​ው​ንም የሚ​ያ​ነሣ ልብ​ሱን ይጠብ፤ እስከ ማታም ርኩስ ነው። እነ​ር​ሱም በእ​ና​ንተ ዘንድ ርኩ​ሳን ናቸው።
29“በም​ድር ላይም ከሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ እነ​ዚህ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው፤ ሙጭ​ል​ጭላ፥ አይጥ፥ እን​ሽ​ላ​ሊት በየ​ወ​ገኑ፥ 30ኤሊ፥ አዞ፥ ገበሎ፥ አር​ጃኖ፥ እስ​ስት። 31ከሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሱት ሁሉ በእ​ና​ንተ ዘንድ ርኩ​ሳን የሚ​ሆኑ እነ​ዚህ ናቸው። ከእ​ነ​ር​ሱም በድ​ና​ቸ​ውን የሚ​ነካ ሁሉ እስከ ማታ ርኩስ ነው። 32ከእ​ነ​ር​ሱም በድ​ና​ቸው በም​ንም ላይ ቢወ​ድቅ እርሱ ርኩስ ነው፤ የዕ​ን​ጨት ዕቃ ወይም ልብስ ወይም ቍር​በት ወይም ከረ​ጢት ቢሆን የሚ​ሠ​ራ​በት ዕቃ ሁሉ እር​ሱን በውኃ ውስጥ ይን​ከ​ሩት፤ እስከ ማታም ርኩስ ነው፤ ከዚ​ያም በኋላ ንጹሕ ይሆ​ናል። 33ከእ​ነ​ር​ሱም አን​ዳች በው​ስጡ የወ​ደ​ቀ​በ​ትን የሸ​ክ​ላ​ውን ዕቃ ሁሉ ስበ​ሩት፤ በው​ስ​ጡም ያለው ሁሉ ርኩስ ነው። 34በእ​ርሱ ውስጥ ያለው፤ ውኃም የሚ​ፈ​ስ​ስ​በት፥ የሚ​በላ መብል ሁሉ ርኩስ ነው፤ በዚ​ህም ዕቃ ሁሉ ያለው የሚ​ጠጣ መጠጥ ሁሉ ርኩስ ነው። 35ከእ​ነ​ዚ​ህም በድን የሚ​ወ​ድ​ቅ​በት ሁሉ ርኩስ ነው፤ እቶን ወይም ምድጃ ቢሆን ይሰ​ባ​በ​ራል፤ ርኩ​ሳን ናቸ​ውና፤ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ይሆ​ናሉ። 36ነገር ግን ምንጩ፥ ጉድ​ጓ​ዱም፥ የው​ኃ​ውም ኵሬ ንጹ​ሓን ናቸው፤ በድ​ና​ቸ​ውን ግን የሚ​ነካ ርኩስ ነው። 37ከበ​ድ​ና​ቸ​ውም በሚ​ዘራ ዘር ላይ አን​ዳች ቢው​ድቅ እርሱ ንጹሕ ነው። 38ነገር ግን በዘሩ ላይ ውኃ ቢፈ​ስ​ስ​በት፥ ከዚህ በኋላ ከበ​ድ​ና​ቸው አን​ዳች ቢወ​ድ​ቅ​በት፥ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው።
39“ለመ​ብል ከሚ​ሆ​ኑ​ላ​ችሁ እን​ስ​ሳት የሞተ ቢኖር፥ በድ​ኑን የሚ​ነካ ሁሉ እስከ ማታ ርኩስ ነው። 40ከበ​ድ​ኑም የሚ​በላ ልብ​ሱን ያጥ​ባል፤ እስከ ማታም ርኩስ ይሆ​ናል፤ በድ​ኑ​ንም የሚ​ያ​ነሣ፤ ልብ​ሱን ይጠብ፥ እስከ ማታም ርኩስ ነው።
41“በም​ድ​ርም ላይ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ አውሬ ሁሉ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው፤ አት​ብ​ሉ​ትም። 42በሆዱ የሚ​ሳብ፥ በአ​ራ​ትም እግ​ሮች የሚ​ሳብ፥ ብዙ እግ​ሮ​ችም ያሉት፥ በም​ድ​ርም ላይ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀሱ ተን​ቀ​ሳ​ቃ​ሾች ሁሉ ርኩ​ሳን ናቸ​ውና አት​ብ​ሉ​አ​ቸው። 43በም​ድር ላይ በሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀሱ ተን​ቀ​ሳ​ቃ​ሾች ሁሉ ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን አታ​ር​ክሱ፤ በእ​ነ​ር​ሱም እን​ዳ​ት​ረ​ክሱ ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን አታ​ር​ክ​ሱ​ባ​ቸው። 44እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝና፤ ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን ቀድሱ፤ ቅዱ​ሳ​ንም ሁኑ፤ እኔ አም​ላ​ካ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቅዱስ ነኝና፤ 45በም​ድ​ርም ላይ በሚ​ሳብ ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ ሁሉ ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን አታ​ሳ​ድፉ። እኔ አም​ላ​ካ​ችሁ እሆን ዘንድ ከግ​ብፅ ምድር ያወ​ጣ​ኋ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ፤ እን​ግ​ዲህ እኔ ቅዱስ ነኝና እና​ን​ተም ቅዱ​ሳን ሁኑ።
46“የእ​ን​ስ​ሳና የወፍ፥ በው​ኃ​ውም ውስጥ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ የፍ​ጥ​ረት ሁሉ፥ በም​ድ​ርም ላይ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ የፍ​ጥ​ረት ሁሉ ሕግ ይህ ነው። 47በር​ኩ​ስና በን​ጹሕ መካ​ከል፥ የሕ​ይ​ወት ነፍስ ካላ​ቸ​ውም በም​ት​በ​ሉ​ትና በማ​ት​በ​ሉት መካ​ከል እን​ድ​ት​ለዩ ነው።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ