መጽ​ሐፈ ኢዮብ 32

32
1ኢዮ​ብም በፊ​ታ​ቸው ራሱን ጻድቅ አድ​ርጎ ነበ​ርና እነ​ዚያ ሦስቱ ወዳ​ጆቹ ለኢ​ዮብ ለመ​መ​ለስ ዝም አሉ። 2ከአ​ው​ስ​ጢድ ሀገር ከአ​ራም ወገን የሆነ የቡ​ዛ​ዊው የባ​ር​ክ​ኤል ልጅ ኤሊ​ዩስ ተቈጣ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት#ግሪክ ሰባ. ሊ. እና ዕብ. “ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይልቅ” ይላሉ። ራሱን ጻድቅ አድ​ርጎ ነበ​ርና ኢዮ​ብን ተቈ​ጣው። 3ደግ​ሞም እንደ ኀጢ​አ​ተኛ አደ​ረ​ጉት እንጂ ለኢ​ዮብ የሚ​ገባ መልስ መመ​ለስ ስላ​ል​ቻሉ በሦ​ስቱ ባል​ን​ጀ​ሮቹ ላይ ተቈጣ። 4ኤሊ​ዩስ ግን ከእ​ርሱ ይልቅ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ነበ​ሩና ለኢ​ዮብ መልስ ለመ​ስ​ጠት ጠብቆ ነበር። 5ኤሊ​ዩ​ስም በእ​ነ​ዚህ በሦ​ስቱ ሰዎች አፍ መልስ እን​ደ​ሌለ ባየ ጊዜ በቍ​ጣው ተቈ​ጣ​ቸው። 6የቡ​ዛ​ዊው የባ​ር​ክ​ኤል ልጅ ኤል​ዩ​ስም መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፥ “እኔ በዕ​ድ​ሜዬ ታናሽ ነኝ፥ እና​ንተ ግን ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ናችሁ፤ ስለ​ዚ​ህም ዕው​ቀ​ቴን እገ​ል​ጥ​ላ​ችሁ ዘንድ ፈርቼ ዝም አልሁ።
7እን​ደ​ዚ​ህም አልሁ፥ “የሚ​ና​ገሩ ዓመ​ታት አይ​ደ​ሉም፥
በዓ​መ​ታት ብዛት ሰዎች ጥበ​ብን አያ​ው​ቋ​ትም።
8ነገር ግን በሟች ሰው ውስጥ መን​ፈስ አለ፥
ሁሉን የሚ​ችል የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ፈ​ስም ያስ​ተ​ም​ራል።
9በዕ​ድሜ ያረጁ ጠቢ​ባን አይ​ደ​ሉም፥
ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችም ፍር​ድን አያ​ስ​ተ​ው​ሉም።
10ነገር ግን፦ ስሙኝ፤
እኔ ደግሞ የማ​ው​ቀ​ውን እገ​ል​ጥ​ላ​ች​ኋ​ለሁ አልሁ።
11እነሆ፥ ንግ​ግ​ሬን አድ​ም​ጡኝ፤
የም​ት​ና​ገ​ሩ​ትን ነገር እስ​ክ​ት​መ​ረ​ምሩ ድረስ
እየ​ሰ​ማ​ች​ሁት እነ​ግ​ራ​ች​ኋ​ለሁ።
12እን​ዲ​ሁም ልብ አደ​ረ​ግሁ፤
እነ​ሆም፥ ከእ​ና​ንተ መካ​ከል ኢዮ​ብን የገ​ሠጸ፥
ወይም ለተ​ና​ገ​ረው ቃልን የመ​ለሰ የለም።
13እና​ን​ተም፦ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበ​ብን አግ​ኝ​ተ​ናል፤
አብ​ዝ​ተ​ና​ልም እን​ዳ​ትሉ ተጠ​ን​ቀቁ።
14እና​ንተ ግን እን​ዲህ ያለ ነገር እን​ዲ​ና​ገር
ለሰው መብት ሰጣ​ች​ሁት።
15“እና​ንተ ፈራ​ችሁ፥ ዳግ​መ​ኛም አል​መ​ለ​ሳ​ች​ሁም፤
ከአ​ፋ​ች​ሁም ቁም ነገር ጠፋ።
16እኔ በት​ዕ​ግ​ሥት ጠበ​ቅሁ እንጂ አል​ተ​ና​ገ​ር​ሁም።
እና​ንተ ዝም ብላ​ችሁ ቆማ​ችሁ፥ አል​መ​ለ​ሳ​ች​ሁ​ምና።”#ግሪክ ሰባ. ሊ. በሦ​ስ​ተኛ መደብ ይጽ​ፋል።
17ኤል​ዩ​ስም መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦
“ደግሜ እና​ገ​ራ​ለሁ።
18እኔ ቃል ተሞ​ል​ቻ​ለ​ሁና፥
በው​ስ​ጤም ያለ መን​ፈስ አስ​ጨ​ን​ቆ​ኛ​ልና።
19በተሃ ጠጅ እንደ ተሞ​ላና ሊቀ​ደድ እንደ ቀረበ አቁ​ማዳ፥
ወይም እንደ አን​ጥ​ረኛ ወናፍ እነሆ፥ አን​ጀቴ ሆነ።
20ጥቂት እን​ድ​ተ​ነ​ፍስ እና​ገ​ራ​ለሁ።
ከን​ፈ​ሬ​ንም ገልጬ እመ​ል​ሳ​ለሁ።
21ከሰው የተ​ነሣ አላ​ፍ​ር​ምና፥
ከሟች ሰውም የተ​ነሣ አላ​ፈ​ገ​ፍ​ግ​ምና።
22ለሰው ፊት ማድ​ላ​ትን አላ​ው​ቅም፤
ከሰ​ውም የተ​ነሣ የማ​ፍ​ረው ካለ ትሎች ይብ​ሉኝ።#ምዕ. 32 ቍ. 22 ከዕ​ብ​ራ​ይ​ስጡ ልዩ​ነት አለው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ