መጽ​ሐፈ ኢዮብ 28

28
1“በእ​ው​ነቱ ብር የሚ​ወ​ጣ​በት ቦታ አለ፥
ወር​ቅም የሚ​ነ​ጠ​ር​በት ስፍራ አለ።
2ብረ​ትም ከመ​ሬት ውስጥ ይወ​ጣል፤
መዳ​ብም እንደ ድን​ጋይ ይፈ​ለ​ጣል።
3ለጨ​ለማ ወሰ​ንን ያደ​ር​ጋል፤
እርሱ ሁሉን ይመ​ረ​ም​ራል፥
የጨ​ለ​ማ​ንና የሞት ጥላ ድን​ጋ​ይ​ንም ይመ​ረ​ም​ራል።
4በአ​ፈር ምክ​ን​ያት እን​ደ​ሚ​ከ​ፈል ወንዝ
የጽ​ድ​ቅን መን​ገድ የረሱ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ይደ​ክ​ማሉ።
ከሰ​ዎ​ችም መካ​ከል ይለ​ያሉ። #በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ልዩ​ነት አለው።
5እን​ጀራ ከም​ድር ውስጥ ይወ​ጣል፤
በእ​ሳ​ትም እን​ደ​ሚ​ሆን ታች​ኛው ይገ​ለ​በ​ጣል።
6ድን​ጋ​ይዋ እንደ ሰን​ፔር፥
ወር​ቅ​ዋም እንደ አፈር የሆነ መሬት አለች።
7መን​ገ​ድ​ዋን ዎፍ አያ​ው​ቀ​ውም፥
የን​ስ​ርም ዐይን አላ​የ​ውም።
8የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ልጆች አል​ረ​ገ​ጡ​አ​ትም፥
ደቦል አን​በ​ሳም በው​ስ​ጥዋ አላ​ለ​ፈ​ባ​ትም።
9ሰው ወደ ቡላድ ድን​ጋይ እጁን ይዘ​ረ​ጋል፥
ተራ​ራ​ዎ​ች​ንም ከመ​ሠ​ረ​ታ​ቸው ይገ​ለ​ብ​ጣ​ቸ​ዋል።
10ከድ​ን​ጋይ ውስጥ መን​ዶ​ል​ዶያ ይወ​ቅ​ራል፤
ዐይ​ኔም የከ​በ​ረ​ውን ነገር ሁሉ ታያ​ለች።
11የፈ​ሳ​ሹ​ንም ጥል​ቀት ይገ​ል​ጣል።
ኀይ​ሉ​ንም በብ​ር​ሃን ይገ​ል​ጣል።
12“ነገር ግን ጥበብ ወዴት ትገ​ኛ​ለች?
የጥ​በ​ብስ ሀገ​ርዋ ወዴት ነው?
13ሟች ሰው መን​ገ​ድ​ዋን አያ​ው​ቅም፤
በሰ​ዎ​ችም ዘንድ አት​ገ​ኝም።
14ቀላይ፦ በእኔ ውስጥ የለ​ችም ትላ​ለች።
ባሕ​ርም፦ በእኔ ዘንድ የለ​ችም ይላል።
15ስለ እር​ስ​ዋም ማንም ምዝ​ምዝ ወርቅ አይ​ሰ​ጥም
ብርም በእ​ር​ስዋ ለውጥ አይ​መ​ዘ​ንም።
16ከአ​ፌር ወር​ቅም ጋር አት​ወ​ዳ​ደ​ርም።
በከ​በረ መረ​ግ​ድና በሰ​ን​ፔር አት​ገ​መ​ትም።
17ወር​ቅና ብር​ጭቆ አይ​ወ​ዳ​ደ​ሩ​አ​ትም፥
የወ​ር​ቅም ጥሬ ዕቃ የእ​ር​ስዋ ለውጥ አይ​ሆ​ንም።
18ዛጎ​ልና አል​ማዝ አይ​ታ​ሰ​ቡም።
አንተ ግን እጅግ ከከ​በሩ ነገ​ሮች ሁሉ ይልቅ
ጥበ​ብን አቅ​ር​ባት።
19የኢ​ት​ዮ​ጵያ ሉል አይ​ተ​ካ​ከ​ላ​ትም፥
በጥ​ሩም ወርቅ አት​ገ​መ​ትም።
20“እን​ግ​ዲያ ጥበብ ከወ​ዴት ትገ​ኛ​ለች?
የማ​ስ​ተ​ዋ​ልስ ሀገሯ ወዴት ነው?
21በሰው ሁሉ ዘንድ ተረ​ስ​ታ​ለች፥
ከሰ​ማይ ወፎ​ችም ተሰ​ው​ራ​ለች።
22ሞትና ሲኦል ወሬ​ዋን በጆ​ሮ​ቻ​ችን ሰማን ብለ​ዋል።
23“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገ​ድ​ዋን አሳ​መረ፥
እር​ሱም ስፍ​ራ​ዋን ያው​ቃል።
24እር​ሱም በሰ​ማይ ያለ​ውን ይመ​ለ​ከ​ታል፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከሰ​ማይ በታች ያለ​ውን ሁሉ ...” ይላል።
በም​ድ​ርም ያለ​ውን ሁሉ ያው​ቃል።
25ለነ​ፋስ ሚዛ​ንን
ለው​ሆ​ችም መስ​ፈ​ሪ​ያን አደ​ረገ።
26እነ​ዚ​ህን በፈ​ጠረ ጊዜ እን​ዲሁ ዐውቆ ቈጠ​ራ​ቸው።
ለዝ​ናም ሥር​ዐ​ትን ለነ​ጐ​ድ​ጓድ መብ​ረ​ቅም መን​ገ​ድን አደ​ረገ።
27በዚ​ያን ጊዜ አያት፥ ገለ​ጣ​ትም፤
አዘ​ጋ​ጃ​ትም፥ አከ​በ​ራት፥ ደግ​ሞም መረ​መ​ራት።
28ሰው​ንም፦ ‘እነሆ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ጥበብ ነው፤
ከክፉ መራ​ቅም ማስ​ተ​ዋል ነው’ ” አለው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ