መጽ​ሐፈ ኢዮብ 27

27
1ኢዮ​ብም ምሳ​ሌ​ውን ይመ​ስል ዘንድ ደገመ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“እን​ደ​ዚህ የፈ​ረ​ደ​ብኝ ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን!
ነፍ​ሴ​ንም መራራ ያደ​ረገ ሁሉን የሚ​ችል ሕያው አም​ላ​ክን!
3እስ​ት​ን​ፋሴ በእኔ ውስጥ ገና ሳለች፥
የሚ​ያ​ና​ግ​ረ​ኝም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ፈስ በአ​ፍ​ን​ጫዬ ውስጥ ገና ሳለ፥
4አን​ደ​በቴ ዐመ​ፅን አይ​ና​ገ​ርም፤
ነፍ​ሴም የዐ​መፅ አሳ​ብን አት​ማ​ርም፤
5እና​ን​ተን ማጽ​ደቅ ከእኔ ዘንድ ይራቅ፤
እስ​ክ​ሞ​ትም ድረስ ፍጹ​ም​ነ​ቴን ከእኔ አላ​ር​ቅ​ምና።
6ጽድ​ቅን እየ​ሠ​ራሁ አል​ጠ​ፋም፤
ያደ​ረ​ግ​ሁት ክፉ ነገር አይ​ታ​ወ​ቀ​ኝ​ምና።
7ጠላ​ቶች እንደ ኀጢ​አ​ተ​ኞች ውድ​ቀት፥
በእኔ ላይም የሚ​ነሡ እንደ በደ​ለ​ኞች ጥፋት ይሁኑ።
8“ኀጢ​አ​ተኛ ድኅ​ነ​ትን ተስፋ ያደ​ርግ ዘንድ ለምን ደጅ ይጠ​ናል?
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርስ የማ​ያ​ምን ይድ​ና​ልን? እንጃ!#በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ታላቅ ልዩ​ነት አለው።
9በውኑ መከራ በመ​ጣ​በ​ትስ ጊዜ፥
ጸሎ​ቱን ይሰ​ማ​ዋ​ልን?
10በእ​ርሱ ዘን​ድስ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ያገ​ኛ​ልን?
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንስ በጠራ ጊዜ ይመ​ል​ስ​ለ​ታ​ልን?
11እኔ ግን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ ምን እን​ዳለ አስ​ተ​ም​ራ​ች​ኋ​ለሁ፤
ሁሉን በሚ​ችል አም​ላክ ዘንድ ያለ​ው​ንም አል​ዋ​ሽም።
12እነሆ፥ ሁላ​ች​ሁም፥
በክ​ፉ​ዎች ላይ ክፋት እን​ደ​ም​ት​መ​ጣ​ባ​ቸው ታው​ቃ​ላ​ችሁ።
13ይህች ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የኀ​ጢ​አ​ተኛ እድል ፋንታ ናት፥
ግፈ​ኞ​ችም ሁሉን ከሚ​ችል አም​ላክ ዘንድ የሚ​ቀ​በ​ሏት ሀብት ናት።
14ልጆቹ ቢበዙ ለጥ​ፋት ይሆ​ናሉ፤
ቢያ​ድ​ጉም ለማ​ኞች ይሆ​ናሉ።
15ለእ​ር​ሱም የቀ​ሩት ፈጽ​መው ይሞ​ታሉ።
ለመ​በ​ለ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም የሚ​ያ​ዝ​ን​ላ​ቸው የለም።
16እርሱ ብርን እንደ አፈር ቢሰ​በ​ስብ፥
ወር​ቅ​ንም እንደ ጭቃ ቢያ​ዘ​ጋጅ፥
17ይህን ሁሉ ጻድ​ቃን ይወ​ስ​ዱ​ታል።
ሀብ​ቱ​ንም ቅኖች ይከ​ፋ​ፈ​ሉ​ታል።
18ቤቱ እንደ ሸረ​ሪት ድር፥
ቅን​ቅ​ንም እን​ደ​ሚ​በ​ላው ይሆ​ናል።
19ባለ​ጠጋ ይተ​ኛል፥ የሚ​ያ​ነ​ቃ​ውም የለም፤#በዕብ. እና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ​ነት አለው።
ዐይ​ኖ​ቹን ይከ​ፍ​ታል፥ ይደ​ነ​ቃ​ልም።
20ሥቃይ እንደ ጎርፍ ታገ​ኘ​ዋ​ለች፤
በሌ​ሊ​ትም ዐውሎ ነፋስ ትነ​ጥ​ቀ​ዋ​ለች።
21የሚ​ያ​ቃ​ጥል ነፋስ ያነ​ሣ​ዋል፥
እር​ሱም ያል​ፋል፤ ከቦ​ታ​ውም ይጠ​ር​ገ​ዋል።
22በእ​ር​ሱም ላይ የማ​ያ​ው​ቀው ይመ​ጣ​በ​ታል፤
አይ​ራ​ራ​ለ​ትም፥ ከእ​ጁም ፈጥኖ መሸሽ ይወ​ድ​ዳል።
23በእ​ር​ሱም እጁን ያጨ​በ​ጭ​ብ​በ​ታል፤
ከስ​ፍ​ራ​ውም በፉ​ጨት ጎትቶ ያወ​ጣ​ዋል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ