የYouVersion አርማ
የፍለጋ አዶ

መጽ​ሐፈ ኢዮብ 23

23
1ኢዮ​ብም መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦
2“ዛሬም ዘለ​ፋዬ ከእጄ እንደ ሆነ ዐወ​ቅሁ።#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ​ነት አለው።
እጁ​ንም በእኔ ላይ አከ​በደ፥ አስ​ለ​ቀ​ሰ​ኝም።
3እር​ሱን ወዴት እን​ደ​ማ​ገ​ኘው ምነው ባወ​ቅሁ!
ወደ ነገሩ ፍጻ​ሜም ምነው በደ​ረ​ስሁ!
4የሠ​ራ​ሁት ቢኖር ይነ​ግ​ረኝ ነበረ፥
ስከ​ራ​ከ​ርም አፌ ዝም አይ​ልም ነበር።
5የሚ​ሰ​ጠ​ኝ​ንም ፈውስ#ዕብ. “የሚ​መ​ል​ስ​ል​ኝን ቃል” ይላል። አውቅ ነበር፥
የሚ​ለ​ኝ​ንም አስ​ተ​ውል ነበር።
6በኀ​ይሉ ብዛት ቢመ​ጣ​ብ​ኝም እንኳ
በቍ​ጣው አያ​ስ​ፈ​ራ​ራ​ኝም ነበር።
7እው​ነ​ትና ቅን​ነት ከእ​ርሱ ዘንድ ናቸ​ውና።
ከፍ​ር​ዴም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያሳ​ር​ፈኝ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፍር​ዴን ያመ​ጣ​ዋል” ይላል። ነበር።
8እነሆ፥ ወደ ፊት እሄ​ዳ​ለሁ፥ እን​ግ​ዲ​ህም አል​ኖ​ርም፤
ስለ ፍጻ​ሜ​ውም አላ​ው​ቅም፤
9ወደ​ሚ​ሠ​ራ​በ​ትም ወደ ግራ ብሄድ አል​መ​ለ​ከ​ተ​ውም፤
ቀኝ እጁ ይከ​ብ​በ​ኛል፤ ነገር ግን አላ​የ​ውም።
10መን​ገ​ዴን ፈጽሞ ዐወቀ፥
እንደ ወር​ቅም ፈተ​ነኝ
11እንደ ትእ​ዛዙ እወ​ጣ​ለሁ፥
መን​ገ​ዱ​ንም ጠብ​ቄ​አ​ለሁ፥ ፈቀ​ቅም አላ​ል​ሁም።
12ከት​እ​ዛ​ዙም አላ​ለ​ፍ​ሁም፤
ቃሉን በልቤ ሰው​ሬ​አ​ለሁ።
13“ስለ ፍርድ የሚ​ከ​ራ​ከር ማን ነው?
እርሱ የወ​ደ​ደ​ውን ያደ​ር​ጋ​ልና።
14ስለ​ዚ​ህም እኔ ስለ እርሱ ቸኰ​ልሁ፤
በተ​ገ​ሠ​ጽ​ሁም ጊዜ አሰ​ብ​ሁት።
15ስለ​ዚህ በፊቱ ደነ​ገ​ጥሁ፤
አስ​በ​ዋ​ለሁ፤ ከእ​ር​ሱም የተ​ነሣ እፈ​ራ​ለሁ።
16እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ልቤን አቀ​ለ​ጠው፥
ሁሉን የሚ​ችል አም​ላ​ክም አስ​ጨ​ን​ቆ​ኛል።
17ጨለ​ማም እን​ደ​ሚ​መ​ጣ​ብኝ፥
ድቅ​ድ​ቁም ጨለማ ፊቴን እን​ደ​ሚ​ከ​ድን አላ​ወ​ቅ​ሁም።

ማድመቅ

Share

Copy

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ