የዮ​ሐ​ንስ ወን​ጌል 19:4-14

የዮ​ሐ​ንስ ወን​ጌል 19:4-14 አማ2000

ጲላ​ጦ​ስም እን​ደ​ገና ወደ ውጭ ወጣና፥ “እነሆ፥ በእ​ርሱ ላይ አን​ዲት በደል ስን​ኳን ያገ​ኘ​ሁ​በት እን​ደ​ሌለ ታውቁ ዘንድ ወደ ውጭ አወ​ጣ​ላ​ች​ኋ​ለሁ” አላ​ቸው። ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም የእ​ሾህ አክ​ሊል ደፍቶ፥ የቀይ ሐር መጐ​ና​ጸ​ፊ​ያም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ፤ ጲላ​ጦ​ስም፥ “እነሆ፥ ሰው​ዬው” አላ​ቸው። ሊቃነ ካህ​ና​ትና ሎሌ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም ባዩት ጊዜ፥ “ስቀ​ለው! ስቀ​ለው!” እያሉ ጮሁ፤ ጲላ​ጦ​ስም፥ “እና​ንተ ራሳ​ችሁ ውሰ​ዱና ስቀ​ሉት፤ እኔስ በእ​ርሱ ላይ በደል አላ​ገ​ኘ​ሁ​በ​ትም” አላ​ቸው። አይ​ሁ​ድም መል​ሰው፥ “እኛ ሕግ አለን፤ እንደ ሕጋ​ች​ንም ሊሞት ይገ​ባል፤ ራሱን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ልጅ አድ​ር​ጎ​አ​ልና” አሉት። ጲላ​ጦ​ስም ይህን ነገር ሰምቶ እጅግ ፈራ። ደግ​ሞም ወደ ፍርድ አደ​ባ​ባይ ገባና ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን፥ “አንተ ከወ​ዴት ነህ?” አለው፤ ጌታ​ችን ኢየ​ሱስ ግን ምንም አል​መ​ለ​ሰ​ለ​ትም። ጲላ​ጦ​ስም፥ “ለእ​ኔም አት​ነ​ግ​ረ​ኝ​ምን? ልሰ​ቅ​ልህ ሥል​ጣን እንደ አለኝ፥ ወይም ልፈ​ታህ ሥል​ጣን እን​ዳ​ለኝ፥ አታ​ው​ቅ​ምን?” አለው። ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “ከሰ​ማይ ካል​ተ​ሰ​ጠህ በቀር በእኔ ላይ አን​ዳች ሥል​ጣን የለ​ህም፤ ስለ​ዚህ ለአ​ንተ አሳ​ልፎ የሰ​ጠኝ ሰው ታላቅ ኀጢ​ኣት አለ​በት” አለው። ስለ​ዚ​ህም ጲላ​ጦስ ሊፈ​ታው ወድዶ ነበር፤ አይ​ሁድ ግን፥ “ይህን ከፈ​ታ​ኸው የቄ​ሣር ወዳጅ አይ​ደ​ለ​ህም፤ ራሱን ንጉሥ የሚ​ያ​ደ​ርግ ሰው ሁሉ በቄ​ሣር ላይ የሚ​ያ​ምፅ ነውና” ብለው ጮሁ። ጲላ​ጦ​ስም ይህን ሰምቶ ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን ወደ ውጭ አወ​ጣው፤ በዕ​ብ​ራ​ይ​ስ​ጥም ገበታ ተብሎ በሚ​ጠ​ራው “ጸፍ​ጸፍ” በሚ​ሉት ቦታ ላይ በወ​ን​በር ተቀ​መጠ። የፋ​ሲ​ካም የመ​ዘ​ጋ​ጀት ቀን ነበር፤ ጊዜ​ዉም ስድ​ስት ሰዓት ያህል ነበር፤ ጲላ​ጦ​ስም አይ​ሁ​ድን፥ “እነሆ፥ ንጉ​ሣ​ችሁ” አላ​ቸው፤