የሞቱ ዝንቦች የተቀመመውን የዘይት ሽቱ ያገሙታል፤ በስንፍናም ካለ ታላቅ ክብር ይልቅ ትንሽ ጥበብ ትበልጣለች። የጠቢብ ልብ በስተቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተግራው ነው። ደግሞም ሰነፍ በልቡ ፈቃድና መንገድ በሚሄድ ጊዜ አእምሮ ይጐድለዋል፥ የሚያስበውም ሁሉ ሰንፍና ነው። ትዕግሥት ታላቁን ኀጢአት ያስተሰርያልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ። ከፀሓይ በታች ያየሁት ክፉ ነገር አለ፥ እርሱም ከገዢ ባለማወቅ የሚወጣ ስሕተት ነው፥ ሰነፍ በታላቅ ማዕርግ ላይ ተሾመ፥ ባለጠጎች ግን በተዋረደ ስፍራ ተቀመጡ። አገልጋዮች በፈረስ ላይ ሲቀመጡ፥ መኳንንትም እንደ አገልጋዮች በምድር ላይ በእግራቸው ሲሄዱ አየሁ። ለባልንጀራው ጕድጓድን የሚምስ ይወድቅበታል፥ ቅጥርንም የሚያፈርስን እባብ ትነድፈዋለች። ድንጋይን የሚፈነቅል ይታመምበታል፥ ዕንጨትንም የሚፈልጥ ይጐዳበታል።
መጽሐፈ መክብብ 10 ያንብቡ
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: መጽሐፈ መክብብ 10:1-9
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች