መጽ​ሐፈ ባሮክ 4

4
1የዘ​ላ​ለም ሕግ የሆነ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የት​እ​ዛዙ መጽ​ሐፍ ይህ ነው፤ የሚ​ጠ​ብ​ቋ​ትም ሁሉ ይኖ​ራሉ፤ የሚ​ተ​ዉ​ኣት ግን ይሞ​ታሉ። 2ያዕ​ቆብ! ተመ​ል​ሰህ ያዛት፤ በብ​ር​ሃ​ን​ዋም ሂድ። 3ክብ​ር​ህን ለባ​ዕድ አት​ስጥ፤ የሚ​ሻ​ል​ህ​ንም ለሌላ ወገን አት​ስጥ። 4የአ​ም​ላ​ካ​ችን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምሕ​ረት በእኛ ታው​ቋ​ልና እኛ እስ​ራ​ኤል ብፁ​ዓን ነን።
መጽ​ና​ናት ለእ​ስ​ራ​ኤል
5ወገ​ኖች ተጽ​ናኑ፤ እስ​ራ​ኤ​ልም አስቡ። 6ለጥ​ፋት ያይ​ደለ ለሌላ ወገን ተሽ​ጣ​ችሁ ነበር፤ ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስላ​ስ​ቈ​ጣ​ች​ሁት ለጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ ተላ​ል​ፋ​ችሁ ተሰ​ጥ​ታ​ችሁ ነበር። 7ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያይ​ደለ ለአ​ጋ​ን​ንት በመ​ሠ​ዋ​ታ​ችሁ ፈጣ​ሪ​ያ​ች​ሁን ለመ​ዓት አነ​ሳ​ሳ​ች​ሁት። 8ያሳ​ደ​ጋ​ች​ሁን የዘ​ለ​ዓ​ለም አም​ላ​ካ​ች​ሁ​ንም ረስ​ታ​ች​ሁ​ታ​ልና፥ ሞግ​ዚ​ታ​ች​ሁን ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም አሳ​ዝ​ና​ች​ኋ​ታ​ልና። 9የመ​ጣ​ባ​ች​ሁን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መቅ​ሠ​ፍት ባየች ጊዜ እን​ዲህ አለች፦ የጽ​ዮን ስደ​ተ​ኞች ስሙ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጽኑፅ ልቅ​ሶን አም​ጥ​ቶ​ብ​ኛ​ልና። 10ዘለ​ዓ​ለ​ማዊ አም​ላክ ያመ​ጣ​ባ​ቸ​ውን የወ​ን​ዶች ልጆ​ች​ንና የሴ​ቶች ልጆ​ችን መማ​ረክ አይ​ቻ​ለ​ሁና 11በደ​ስታ አሳ​ድ​ጊ​ያ​ቸው ነበር፤ ነገር ግን በል​ቅ​ሶና በኀ​ዘን ሸኘ​ኋ​ቸው። 12በብ​ዙ​ዎች ዘንድ የተ​ጣ​ልሁ በሆ​ንሁ በእኔ በመ​በ​ለ​ቲቱ ደስ የሚ​ለው አይ​ኑር፤ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ርቀ​ዋ​ልና። 13ትእ​ዛ​ዙ​ንም አላ​ወ​ቋ​ትም፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በት​እ​ዛዙ መን​ገድ አል​ተ​መ​ላ​ለ​ሱም፤ በም​ክ​ሩም ፍለጋ ወደ ጽድቁ አል​ገ​ቡም።
14የጽ​ዮን ስደ​ተ​ኞች ይምጡ፤ ዘለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው አም​ላክ ያመ​ጣ​ባ​ቸ​ውን የወ​ን​ዶች ልጆ​ች​ንና የሴ​ቶች ልጆ​ች​ንም ምርኮ ያስቡ። 15የማ​ያ​ፍ​ርና ቋን​ቋው ልዩ የሆነ ሕዝ​ብን ከሩቅ አም​ጥ​ቶ​ባ​ቸ​ዋ​ልና፤ ሽማ​ግ​ሌ​ውን አላ​ከ​በ​ሩ​ምና፥ ለሕ​ፃ​ና​ቱም አል​ራ​ሩ​ምና። 16የመ​በ​ለ​ት​ነ​ቷ​ንም የተ​ወ​ደዱ ልጆች ነጠቁ፤ ከሴ​ቶች ልጆ​ች​ዋም ለይ​ተው ብቻ​ዋን አስ​ቀ​ሩ​አት። 17ነገር ግን እኔ ምን ረዳ​ች​ኋ​ለሁ? 18ክፉ ነገ​ርን ያመ​ጣ​ባ​ችሁ እርሱ ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ እጆች ያወ​ጣ​ች​ኋ​ልና። 19ልጆች! መን​ገ​ዳ​ች​ሁን ሂዱ፤ መን​ገ​ዳ​ች​ሁን ሂዱ፤ እኔ የተ​ፈ​ታች ምድረ በዳ ሁኛ​ለ​ሁና። 20የሰ​ላም ልብ​ሴን አወ​ለ​ቅሁ፤ የመ​ከ​ራ​ዬ​ንም ማቅ ለበ​ስሁ፤ በዘ​መ​ኔም ወደ ዘለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው አም​ላክ እጮ​ሃ​ለሁ፤
21ልጆች ተጽ​ናኑ፤ ወደ አም​ላ​ክም ጩኹ፤ ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ እጅና አገ​ዛዝ ያወ​ጣ​ች​ኋል። 22ከዘ​ለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው አም​ላክ ዘንድ ድኅ​ነ​ታ​ች​ሁን ተስፋ አድ​ር​ጌ​አ​ለ​ሁና። ከዘ​ለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው መድ​ኀ​ኒ​ታ​ችን ዘንድ ፈጥኖ ስለ​ሚ​መ​ጣ​ላ​ችሁ ምሕ​ረ​ትም ደስታ ከቅ​ዱሱ መጣ​ልኝ፤ 23ከኀ​ዘ​ንና ከል​ቅሶ ጋር ሸኝ​ቻ​ች​ኋ​ለ​ሁና፤ ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እና​ን​ተን በደ​ስ​ታና በሐ​ሤት ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይመ​ል​ስ​ል​ኛል። 24የጽ​ዮን ጎረ​ቤ​ቶች መማ​ረ​ካ​ች​ሁን እን​ዳዩ፥ እን​ዲ​ሁም በታ​ላቅ ክብ​ርና በዘ​ለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው አም​ላክ ብር​ሃን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የም​ት​መ​ጣ​ላ​ች​ሁን ድኅ​ነ​ታ​ች​ሁን ፈጥ​ነው ያያሉ።
25ልጆች! ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የመ​ጣ​ባ​ች​ሁን ቍጣ በት​ዕ​ግ​ሥት ተቀ​በሉ፤ ጠላ​ቶ​ቻ​ችሁ አሳ​ድ​ደ​ዋ​ች​ኋ​ልና ውድ​ቀ​ታ​ቸ​ውን ፈጥ​ና​ችሁ ታያ​ላ​ችሁ፤ በራ​ሳ​ቸ​ውም ላይ ትወ​ጣ​ላ​ችሁ። 26ቅም​ጥ​ሎች በሻ​ካ​ረው መን​ገድ ሄዱ፤ ጠላ​ቶ​ችም እንደ ተዘ​ረፉ በጎች ነጠ​ቋ​ቸው። 27ልጆች! ተጽ​ናኑ፤ ወደ አም​ላ​ክም ጩኹ፤ የወ​ሰ​ዳ​ችሁ እርሱ ያስ​ባ​ች​ኋል። 28ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትርቁ ዘንድ ፈቃ​ዳ​ችሁ እንደ ሆነ እን​ዲሁ ዐሥር ጊዜ ወደ​ኋላ ተመ​ል​ሳ​ችሁ ትፈ​ል​ጉ​ታ​ላ​ችሁ፤ 29ይህን መቅ​ሠ​ፍት ያመ​ጣ​ባ​ችሁ እርሱ ዘለ​ዓ​ለ​ማዊ ደስ​ታን ከድ​ኅ​ነ​ታ​ችሁ ጋር ዳግ​መኛ ያመ​ጣ​ላ​ች​ኋል።
የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ረድ​ኤት እንደ ተረ​ጋ​ገጠ
30ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ተጽ​ናኚ፤ ስም ያወ​ጣ​ልሽ እርሱ ያጽ​ና​ና​ሻል። 31መከራ ያጸ​ኑ​ብ​ሽና በው​ድ​ቀ​ት​ሽም ደስ ያላ​ቸው ይጐ​ሰ​ቍ​ላሉ። 32ልጆ​ች​ሽን የገዙ፥ ልጆ​ች​ሽ​ንም ማር​ከው የወ​ሰዱ ከተ​ሞች ይጐ​ሰ​ቍ​ላሉ። 33በጥ​ፋ​ትሽ ደስ እንደ አላት፥ በው​ድ​ቀ​ት​ሽም ሐሤት እንደ አደ​ረ​ገች እን​ዲሁ በራ​ስዋ ጥፋት ታዝ​ና​ለች። 34ብዙ ደስ​ታ​ዋ​ንም ከእ​ር​ስዋ አስ​ወ​ግ​ዳ​ለሁ፤ ደስ​ታ​ዋም ወደ ኀዘን ይመ​ለ​ሳል። 35እሳት ከዘ​ለ​ዓ​ለ​ማ​ዊው አም​ላክ ለረ​ዥም ዘመን ይመ​ጣ​ባ​ታ​ልና ለብዙ ዘመ​ንም የአ​ጋ​ን​ንት ማደ​ሪያ ትሆ​ና​ለ​ችና። 36ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ወደ ምሥ​ራቅ ተመ​ል​ከች ከአ​ም​ላ​ክሽ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ጣ​ልሽ ደስ​ታ​ንም እዪ። 37እነሆ የላ​ክ​ሻ​ቸው ልጆ​ችሽ መጡ፤ በቅ​ዱ​ሱም ቃል ከም​ሥ​ራ​ቅና ምዕ​ራብ ተሰ​በ​ሰቡ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ክብር ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ