የሐ​ዋ​ር​ያት ሥራ 10:34-48

የሐ​ዋ​ር​ያት ሥራ 10:34-48 አማ2000

ጴጥ​ሮ​ስም አፉን ከፈ​ተና እን​ዲህ አለ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሰው ፊት እን​ደ​ማ​ያ​ዳላ በእ​ው​ነት አየሁ። ነገር ግን በሕ​ዝብ ሁሉ ዘንድ እር​ሱን የሚ​ፈ​ራና እው​ነ​ትን የሚ​ያ​ደ​ርግ በእ​ርሱ ዘንድ የተ​ወ​ደደ ነው። ቃሉን ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ላከ፤ በኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶ​ስም ሰላ​ምን ነገ​ራ​ቸው፤ እር​ሱም የሁሉ ገዢ ነው። ዮሐ​ንስ ከሰ​በ​ከው ጥም​ቀት በኋላ ከገ​ሊላ ጀምሮ በይ​ሁዳ የሆ​ነ​ውን ነገር ሁሉ እና​ንተ ራሳ​ችሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ። ስለ ናዝ​ሬቱ ስለ ኢየ​ሱስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ን​ፈስ ቅዱስ በኀ​ይ​ልም እንደ ቀባው፥ እየ​ዞ​ረም መል​ካም እንደ አደ​ረገ፥ ሰይ​ጣን ያሸ​ነ​ፋ​ቸ​ው​ንም እንደ ፈወሰ ታው​ቃ​ላ​ችሁ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ርሱ ጋር ነበ​ርና። በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባደ​ረ​ገ​ውም ሁሉ እኛ ምስ​ክ​ሮች ነን፤ እር​ሱ​ንም በዕ​ን​ጨት ላይ ሰቅ​ለው ገደ​ሉት። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን በሦ​ስ​ተ​ኛው ቀን ከሙ​ታን ለይቶ አስ​ነ​ሣው፤ በግ​ልጥ እን​ዲ​ታ​ይም አደ​ረ​ገው። ይኸ​ውም ለሕ​ዝቡ ሁሉ አይ​ደ​ለም፤ ነገር ግን አስ​ቀ​ድሞ ለመ​ረ​ጣ​ቸ​ውና ምስ​ክ​ሮች ለሚ​ሆ​ኑት ብቻ ነው እንጂ፤ የመ​ረ​ጣ​ቸው የተ​ባ​ል​ንም እኛ ነን፤ ከሙ​ታ​ንም ተለ​ይቶ ከተ​ነሣ በኋላ ከእ​ርሱ ጋር የበ​ላን የጠ​ጣ​ንም እኛ ነን። በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ በሕ​ያ​ዋ​ንና በሙ​ታን ላይ ፈራጅ ሆኖ የተ​ሾመ እርሱ እንደ ሆነ ለሕ​ዝብ እና​ስ​ተ​ምር ዘንድ አዘ​ዘን። ለሚ​ያ​ም​ኑ​በ​ትም ሁሉ ኀጢ​አ​ታ​ቸው በስሙ እን​ደ​ሚ​ሰ​ረ​ይ​ላ​ቸው ነቢ​ያት ሁሉ ምስ​ክ​ሮቹ ናቸው።” ጴጥ​ሮ​ስም ይህን ነገር ሲነ​ግ​ራ​ቸው ይህን ትም​ህ​ርት በሰ​ሙት ሰዎች ሁሉ ላይ መን​ፈስ ቅዱስ ወረደ። ከጴ​ጥ​ሮስ ጋር የመጡ ከአ​ይ​ሁድ ወገን የሆኑ ምእ​መ​ናን ሁሉ ደነ​ገጡ፤ የመ​ን​ፈስ ቅዱስ ጸጋ በአ​ሕ​ዝብ ላይ ወር​ዶ​አ​ልና። በልዩ ልዩ ሀገር ቋንቋ ሲና​ገሩ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሲያ​መ​ሰ​ግኑ ሰም​ተ​ዋ​ቸ​ዋ​ልና። ጴጥ​ሮ​ስም፥ “እንደ እኛ መን​ፈስ ቅዱ​ስን ከተ​ቀ​በሉ በኋላ እን​ግ​ዲህ በውኃ እን​ዳ​ይ​ጠ​መቁ ውኃን ሊከ​ለ​ክ​ላ​ቸው የሚ​ችል ማነው?” አለ። በኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶ​ስም ስም እን​ዲ​ጠ​መቁ አዘ​ዛ​ቸው። ከዚ​ህም በኋላ ጥቂት ቀን አብ​ሮ​አ​ቸው እን​ዲ​ቀ​መጥ ጴጥ​ሮ​ስን ማለ​ዱት።