መጽ​ሐፈ ሳሙ​ኤል ካልእ 12

12
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በነ​ቢዩ በና​ታን ዳዊ​ትን እንደ ገሠ​ጸው
1እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ነቢዩ ናታ​ንን ወደ ዳዊት ላከ፤ ወደ እር​ሱም መጥቶ አለው፥ “በአ​ንድ ከተማ አንዱ ባለ​ጠጋ፥ አን​ዱም ድሃ የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ። 2ባለ​ጠ​ጋ​ውም እጅግ ብዙ የበ​ግና የላም መንጋ ነበ​ረው። 3ለድ​ሃው ግን ከገ​ዛት አን​ዲት ታናሽ በግ በቀር አን​ዳች አል​ነ​በ​ረ​ውም፤ አሳ​ደ​ጋ​ትም፤ ተን​ከ​ባ​ከ​ባ​ትም፤ ከእ​ር​ሱና ከል​ጆቹ ጋር አደ​ገች፤ ከእ​ን​ጀ​ራ​ውም ትበላ፥ ከዋ​ን​ጫ​ውም ትጠጣ፥ በብ​ብ​ቱም ትተኛ ነበረ፤ እንደ ልጁም ነበ​ረች። 4ወደ ባለ​ጠ​ጋ​ውም እን​ግዳ በመጣ ጊዜ ከበ​ጉና ከላሙ ወስዶ ለዚያ ወደ እርሱ ለመ​ጣው እን​ግዳ ያዘ​ጋ​ጅ​ለት ዘንድ ሳሳ፤ የዚ​ያ​ንም የድ​ሃ​ውን ሰው በግ ወስዶ ለዚያ ለመ​ጣው ሰው አዘ​ጋጀ። 5ዳዊ​ትም በዚያ ሰው ላይ ተቈጣ፤ ዳዊ​ትም ናታ​ንን፥ “ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! ይህን ያደ​ረገ ሰው ሞት የሚ​ገ​ባው ነው። 6ይህን አድ​ር​ጎ​አ​ልና፥ አላ​ዘ​ነ​ምና ስለ አን​ዲቱ በግ አራት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሰባት” ይላል። አድ​ርጎ ይመ​ልስ” አለው።
7ናታ​ንም ዳዊ​ትን አለው፥ “ይህን ያደ​ረገ ያ ሰው አንተ ነህ፤ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ንጉሥ ልት​ሆን ቀባ​ሁህ፤ ከሳ​ኦ​ልም እጅ አዳ​ን​ሁህ፤ 8የጌ​ታ​ህ​ንም ቤት ሰጠ​ሁህ፤ የጌ​ታ​ህ​ንም ሚስ​ቶች በብ​ብ​ትህ ጣል​ሁ​ልህ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንና የይ​ሁ​ዳን ቤት ሰጠ​ሁህ፤ ይህም አንሶ ቢሆን ኖሮ ከዚህ የበ​ለጠ እጨ​ም​ር​ልህ ነበር። 9አሁ​ንስ በፊቱ ክፉ ትሠራ ዘንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ነገር ለምን አቃ​ለ​ልህ? ኬጤ​ያ​ዊ​ውን ኦር​ዮን በሰ​ይፍ መት​ተ​ሃል፤ ሚስ​ቱ​ንም ለአ​ንተ ሚስት ትሆን ዘንድ ወስ​ደ​ሃል፤ እር​ሱ​ንም በአ​ሞን ልጆች ሰይፍ ገድ​ለ​ሃል። 10ስለ​ዚ​ህም አቃ​ል​ለ​ኸ​ኛ​ልና፥ የኬ​ጤ​ያ​ዊ​ው​ንም የኦ​ር​ዮን ሚስት ለአ​ንተ ሚስት ትሆን ዘንድ ወስ​ደ​ሃ​ልና ለዘ​ለ​ዓ​ለም ከቤ​ትህ ሰይፍ አይ​ር​ቅም። 11እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እነሆ ከቤ​ትህ ክፉ ነገ​ርን አስ​ነ​ሣ​ብ​ሃ​ለሁ፤ ሚስ​ቶ​ች​ህ​ንም በዐ​ይ​ኖ​ችህ እያ​የህ እወ​ስ​ዳ​ለሁ፤ ለዘ​መ​ድ​ህም እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በዚ​ችም ፀሐይ ፊት ከሚ​ስ​ቶ​ችህ ጋር ይተ​ኛል። 12አንተ ይህን በስ​ውር አድ​ር​ገ​ኸ​ዋል፤ እኔ ግን ይህን በእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ፊትና በፀ​ሐይ ፊት አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ።” 13ዳዊ​ትም ናታ​ንን፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በድ​ያ​ለሁ” አለው። ናታ​ንም ዳዊ​ትን አለው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ደግሞ ኀጢ​አ​ት​ህን አር​ቆ​ል​ሃል፤ አት​ሞ​ት​ምም። 14ነገር ግን በዚህ ነገር ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጠላ​ቶች መነ​ሣ​ሣት ምክ​ን​ያት አድ​ር​ገ​ሃ​ልና ስለ​ዚህ ደግሞ የተ​ወ​ለ​ደ​ልህ ልጅ ፈጽሞ ይሞ​ታል” አለው። 15ናታ​ንም ወደ ቤቱ ተመ​ለሰ።
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የኦ​ርዮ ሚስት ለዳ​ዊት የወ​ለ​ደ​ች​ውን ሕፃን ቀሠ​ፈው፤ እጅ​ግም ታምሞ ነበር። 16ዳዊ​ትም ስለ ሕፃኑ እግ​ዚ​አ​ሔ​ርን ለመነ፤ ዳዊ​ትም ጾመ፤ ገብ​ቶም በመ​ሬት ላይ ተኛ። 17የቤ​ቱም ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ተነ​ሥ​ተው ከም​ድር ያነ​ሡት ዘንድ በአ​ጠ​ገቡ ቆሙ፤ እርሱ ግን እንቢ አለ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር እን​ጀራ አል​በ​ላም። 18በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ቀን ሕፃኑ ሞተ። የዳ​ዊ​ትም ብላ​ቴ​ኖች፥ “ሕፃኑ በሕ​ይ​ወት ሳለ ብን​ነ​ግ​ረው አል​ሰ​ማ​ንም፤ ይል​ቁ​ንስ ሕፃኑ እንደ ሞተ ብን​ነ​ግ​ረው እን​ዴት ይሆን? በራሱ ላይ ክፉ ያደ​ር​ጋል” ብለው ሕፃኑ እንደ ሞተ ይነ​ግ​ሩት ዘንድ ፈሩ። 19ዳዊ​ትም ብላ​ቴ​ኖቹ በሹ​ክ​ሹ​ክታ ሲነ​ጋ​ገሩ ባየ ጊዜ ዳዊት ሕፃኑ እንደ ሞተ ዐወቀ፤ ዳዊ​ትም ብላ​ቴ​ኖ​ቹን፥ “ሕፃኑ ሞቶ​አል?” አላ​ቸው። እነ​ር​ሱም፥ “ሞቶ​አል” አሉት። 20ዳዊ​ትም ከም​ድር ተነ​ሥቶ ታጠበ፤ ተቀ​ባም፤ ልብ​ሱ​ንም ለወጠ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ገብቶ ሰገደ። ወደ ቤቱም መጣ፦ እን​ጀ​ራም አም​ጡ​ልኝ አለ፤ በፊ​ቱም እን​ጀራ አቀ​ረ​ቡ​ለት፤ በላም። 21ብላ​ቴ​ኖ​ቹም፥ “ይህ ስለ ሕፃኑ ያደ​ረ​ግ​ኸው ነገር ምን​ድን ነው? እርሱ በሕ​ይ​ወት ሳለ ጾም​ህና አለ​ቀ​ስህ፤ እን​ቅ​ል​ፍም አጣህ፤ ሕፃኑ ከሞተ በኋላ ግን ተነ​ሥ​ተህ እን​ጀራ በላህ፤ ጠጣ​ህም” አሉት። 22ዳዊ​ትም፥ “ሕፃኑ ሕያው ሳለ፤ ምና​ል​ባት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይም​ረኝ፥ ሕፃ​ኑም በሕ​ይ​ወት ይኖር እንደ ሆነ ማን ያው​ቃል? ብዬ ጾምሁ፤ አለ​ቀ​ስ​ሁም። 23አሁን ግን ሞቶ​አል፤ የም​ጾ​መው ስለ ምን​ድን ነው? በውኑ እን​ግ​ዲህ እመ​ል​ሰው ዘንድ ይቻ​ለ​ኛ​ልን? እኔ ወደ እርሱ እሄ​ዳ​ለሁ እንጂ እርሱ ወደ እኔ አይ​መ​ለ​ስም” አለ።
24ዳዊ​ትም ሚስ​ቱን ቤር​ሳ​ቤ​ህን አጽ​ና​ናት፤ ወደ እር​ስ​ዋም ገባ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም ጋር ተኛ፤ ፀነ​ሰ​ችም፤ ወንድ ልጅም ወለ​ደች፤ ስሙ​ንም ሰሎ​ሞን ብሎ ጠራው። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ወደ​ደው። 25ደግ​ሞም በነ​ቢዩ በና​ታን እጅ ልኮ ስሙን ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍቁረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር#ዕብ. “ያዴ​ዲያ” ይላል። ብሎ ጠራው።
ዳዊት አሞ​ና​ው​ያ​ንን ድል እንደ አደ​ረገ
(1ዜ.መ. 20፥1-3)
26ኢዮ​አ​ብም የአ​ሞ​ንን ልጆች ከተማ ራባ​ትን ወጋ፤ የመ​ን​ግ​ሥ​ታ​ቸ​ው​ንም ከተማ ያዘ። 27ኢዮ​አ​ብም ወደ ዳዊት እን​ዲህ ብሎ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላከ፥ “ራባ​ትን ወግ​ቻ​ለሁ፤ የው​ኃ​ው​ንም ከተማ ይዤ​አ​ለሁ። 28አሁ​ንም ከተ​ማ​ዪ​ቱን እኔ ቀድሜ እን​ዳ​ል​ይዝ፥ በስ​ሜም እን​ዳ​ት​ጠራ፥ የቀ​ረ​ውን ሕዝብ ሰብ​ስብ፥ ከተ​ማ​ዪ​ቱ​ንም ከብ​በህ ቀድ​መህ ያዛት።” 29ዳዊ​ትም ሕዝ​ቡን ሁሉ ሰብ​ስቦ ወደ ራባት ሄደ፤ ወግ​ቶም ያዛት። 30የን​ጉ​ሣ​ቸ​ው​ንም የሜ​ል​ኮ​ምን ዘውድ ከራሱ ላይ ወሰደ። ክብ​ደ​ቱም አንድ መክ​ሊት ወርቅ ያህል ነበር፤ ክቡር ዕን​ቍም ነበ​ረ​በት፤ ዳዊ​ትም በራሱ ላይ አደ​ረ​ገው። ከከ​ተ​ማ​ዪ​ቱም እጅግ ብዙ ምርኮ አወጣ። 31በው​ስ​ጥ​ዋም የነ​በ​ሩ​ትን ሕዝብ አው​ጥቶ በመ​ጋ​ዝና በብ​ረት መቈ​ፈ​ሪያ በብ​ረት መጥ​ረ​ቢ​ያም ሥር አኖ​ራ​ቸው፤ በሸ​ክላ ጡብ እቶ​ንም አሳ​ለ​ፋ​ቸው።#ዕብ. “በመ​ጋ​ዝና በብ​ረት መቈ​ፈ​ሪያ፥ በመ​ጥ​ረ​ቢ​ያም እን​ዲ​ሠሩ አደ​ረ​ጋ​ቸው” ይላል። በአ​ሞን ልጆች ከተ​ሞች ሁሉ እን​ዲሁ አደ​ረገ። ዳዊ​ትም፥ ሕዝ​ቡም ሁሉ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ተመ​ለሱ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ