የYouVersion አርማ
የፍለጋ አዶ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 3

3
የሦ​ስቱ ጠባ​ቂ​ዎች ውድ​ድር
1ንጉሡ ዳር​ዮ​ስም በመ​ን​ግ​ሥቱ ላሉ ሁሉ ለቤተ ሰዎቹ፥ ለሜ​ዶ​ንና ለፋ​ርስ መኳ​ን​ንት ሁሉ፥ 2ለመ​ሳ​ፍ​ንቱ ሁሉ፥ በሥሩ ለሚ​ገኙ ከሕ​ንድ እስከ ኢት​ዮ​ጵያ ባሉ መቶ ሃያ ሰባት ግዛ​ቶች ላሉ አዛ​ዦ​ችና ሹሞች ሁሉ ታላቅ በዓል አደ​ረገ። 3በል​ተ​ውና ጠጥ​ተ​ውም ጠገቡ፤ ከዚ​ህም በኋላ ወደ ቤታ​ቸው ገቡ፤ ንጉሡ ዳር​ዮ​ስም ወደ እል​ፍኙ ገብቶ ተኛ።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ግን ወዲ​ያው ነቃ” የሚል ይጨ​ም​ራል።
4ንጉ​ሡ​ንም የሚ​ጠ​ብ​ቁት ሦስት ጐል​ማ​ሶች ራስ ጠባ​ቂ​ዎች ነበሩ። እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም እን​ዲህ ተባ​ባሉ፦ 5“ሁላ​ችን የሚ​ያ​ስ​ጐ​መ​ጅና የሚ​ወ​ደድ አን​ዳ​ንድ ቃል አሻ​ሽ​ለን እን​ና​ገር ዘንድ ኑ፤ ነገሩ በጥ​በብ ከባ​ል​ን​ጀ​ራው ለተ​ሻ​ለ​ለት ንጉሡ ዳር​ዮስ ብዙ ስጦታ ይስ​ጠው፤ የአ​ሸ​ና​ፊ​ነ​ቱ​ንም ዋጋ ይስ​ጠው። 6ነጭ ሐርም ያል​ብ​ሰው፤ በወ​ርቅ ጽዋም ይጠጣ፤ በወ​ርቅ አል​ጋም ይተኛ፤ በወ​ርቅ ሰረ​ገ​ላም ላይ ይቀ​መጥ፤ ከተ​ልባ እግ​ርም የተ​ሠራ መጠ​ም​ጠ​ሚያ በራሱ ላይ ያድ​ርግ፤ በአ​ን​ገ​ቱም ላይ ዝር​ግፍ ወርቅ ይሰር። 7ስለ ጥበ​ቡም ከን​ጉሡ ቀጥሎ ይቀ​መጥ፤ የን​ጉ​ሡም ዘመድ ይሁን።”
8ከዚ​ህም በኋላ ሁሉም የየ​ራ​ሳ​ቸ​ውን ቃል ጻፉ፤ አት​መ​ውም ከን​ጉሡ ከዳ​ር​ዮስ መከዳ በታች አኖ​ሩት። 9እን​ዲ​ህም አሉ፥ “ንጉሡ ከዕ​ን​ቅ​ልፉ በነቃ ጊዜ ይህ​ቺን ደብ​ዳቤ እን​ሰ​ጠ​ዋ​ለን፤ ንጉ​ሡና ሦስቱ የፋ​ርስ ሹሞ​ቹም በቃሉ ለተ​ወ​ደ​ደ​ውና ብልህ ለሆ​ነው ይፍ​ረ​ዱ​ለት።” 10አን​ደ​ኛው “ወይን ያሸ​ን​ፋል” ብሎ ጻፈ። 11ሁለ​ተ​ኛ​ውም “ንጉሥ ያሸ​ን​ፋል” ብሎ ጻፈ። 12ሦስ​ተ​ኛ​ውም “ሴቶች ያሸ​ን​ፋሉ፤ ከሁ​ሉም ይልቅ እው​ነት ታሸ​ን​ፋ​ለች” ብሎ ጻፈ።
13ከዚ​ህም በኋላ ዳር​ዮስ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ንጉሡ” ይላል። በነቃ ጊዜ ያቺን መጽ​ሐፍ አን​ሥ​ተው ሰጡት፤ አነ​በ​ባ​ትም። 14በሜ​ዶ​ንና በፋ​ርስ ያሉ አዛ​ዦ​ችን ሁሉ፥ መሳ​ፍ​ን​ቱ​ንና ሹሞ​ቹን፥ አለ​ቆ​ቹ​ንና መኳ​ን​ን​ቱ​ንም ወደ አዳ​ራሹ ይጠሩ ዘንድ ላከ፤ 15በአ​ጠ​ገ​ቡም ተቀ​ም​ጠው ያችን መጽ​ሐፍ በፊ​ታ​ቸው አስ​ነ​በ​ቧት። 16እር​ሱም፥ “እነ​ዚ​ያን ጐል​ማ​ሶች ሰዎች ጥሯ​ቸው፤ እነ​ርሱ ራሳ​ቸው ነገ​ራ​ቸ​ውን ይና​ገሩ” አለ፤ ጠር​ተ​ውም አገ​ቡ​አ​ቸው።
ስለ ወይን አሸ​ና​ፊ​ነት የቀ​ረ​በው ሐተታ
17እን​ዲ​ህም አላ​ቸው፥ “ነገ​ራ​ች​ሁን ተና​ገሩ፥” ወይን ያሸ​ን​ፋል ብሎ መጀ​መ​ሪያ የተ​ና​ገ​ረ​ውም ይና​ገር ጀመር። 18እን​ዲ​ህም አለ፥ “እና​ንተ ሰዎች፥ ወይን የሚ​ጠ​ጣ​ውን ሰው ሁሉ እን​ደ​ሚ​ያ​ሸ​ን​ፈው፥ አእ​ም​ሮ​ው​ንም እን​ደ​ሚ​ያ​ሳ​ጣው አስ​ተ​ውሉ። 19የን​ጉ​ሡ​ንና የድኃ አደ​ጉን፥ የባ​ሪ​ያ​ዉ​ንና የነ​ጻ​ዉን፥ የድ​ኃ​ው​ንና የባ​ለ​ጸ​ጋ​ውን ልቡና አንድ ያደ​ር​ገ​ዋል። 20የሰ​ውን ሁሉ ልቡና ወደ ደስታ መልሶ ደስ ያሰ​ኛ​ቸ​ዋል፤ ኀዘ​ኑ​ንም ሁሉ አያ​ስ​ቡ​ትም፤ ጭን​ቀ​ቱ​ንም ሁሉ አያ​ስ​ቡ​ትም። 21የሰ​ውን ሁሉ ልቡና ባለ ጸጋ ያደ​ር​ገ​ዋል፤ ንጉ​ሡ​ንም አያ​ስ​ቡ​ትም፤ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ው​ንም አያ​ስ​ቡ​ትም #“ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን አያ​ስ​ቡ​ትም” እና “ከባድ ነገር” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ሰው​ንም ሁሉ ከባድ ነገር ያና​ግ​ረ​ዋል። 22በጠ​ጡ​ትም ጊዜ ወዳጅ ወዳ​ጁን፥ ወን​ድ​ምም ወን​ድ​ሙን ይረ​ሳ​ዋል፥ ሾተ​ላ​ቸ​ው​ንም ያማ​ዝ​ዛ​ቸ​ዋል። 23ከስ​ካ​ራ​ቸ​ውም በነቁ ጊዜ ያደ​ረ​ጉ​ትን አያ​ስ​ቡ​ትም። 24እና​ንተ ሰዎች፥ በግድ እን​ዲህ የሚ​ያ​ደ​ር​ገው ወይን አያ​ሸ​ን​ፍ​ምን?” ከዚ​ህም በኋላ እርሱ እን​ዲህ ብሎ ተና​ግሮ ዝም አለ።

ማድመቅ

Share

Copy

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ